በአፍሪካ የኮሮናቫይረስን ፈውስ ለማግኘት እየተደረጉ ካሉ ሙከራዎች በጥቂቱ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የአፍሪካ የበሽታዎች ቁጥጥር ማእከል ከሰሞኑ በአፍሪካ ውስጥ የኮሮናቫይረስን ፈውስ ለማግኘት እየተደረጉ ስላሉ የመድኃኒቶች እንዲሁም የክትባት ሙከራዎች ይፋ አድርጓል።
እስካሁን ባለው መረጃ በአህጉሪቷ ውስጥ በ52 ሃገራት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መኖራቸው ተረጋግጧል፤ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 37ሺህ ደርሷል።
ከሌሎች አህጉራት ጋር ሲነፃፀር በአፍሪካ ውስጥ እየተደረጉ ያሉ ሙከራዎች በቁጥር ትንሽ መሆናቸውን ማእከሉ አስታውቋል።
የማዕከሉ ዶክተር ታጂ ራጁዲን ከጠቀሷቸው ሙከራዎች መካከል፦
- በግብፅ አስራ ሶስት ያህል ሙከራዎች እየተከናወኑ ሲሆን ከነዚህም መካከል ሁለት ክትባት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ ተፈጥሯዊ ንጥረ ነገሮችም ላይ ምርምር በማድረግ ላይ ሲሆኑ ለምሳሌ ማር ምን ያህል የሰውነት በሽታን የመከላከል አቅምን ይጨምራል የሚለውንም በጥልቀት እያጠኑት ነው።
- በዛምቢያ የወባ መድኃኒት በሆነው ሃይድሮክሲክሎሮኪን ላይ ምርምሮች ቀጥለዋል።
- በደቡብ አፍሪካም በክሎሮኪን፣ ኢንተርፌሮንና ሬምዴሲቪር የሚባሉ መድኃኒቶች የኮሮናቫይረስን ይፈውሱት ይሆን የሚሉ ምርምሮች እየተደረጉ ነው።
- በናይጄሪያም እንዲሁ የሰውነትን የማገገም አቅምን መጨመር የሚችሉ ንጥረ ነገሮች ላይ አተኩረዋል።
- በቱኒዝያም ሁለት ሙከራዎች እየተካሄዱ ሲሆን ዝርዝሩ አልተነገረም።
የአፍሪካ የበሽታዎች ቁጥጥር ማዕከል በአህጉሪቷ እየተደረጉ ያሉ ምርምሮችን በማጠናቀር ላይ ሲሆን አህጉሪቷ ተመልካች ብቻ ሳትሆን አስተዋፅኦ ማድረግ እንደምትችልም ለማሳየት ያለመ ነው።














