BBC News, አማርኛ - ዜና
ዜና
የአሜሪካው ልዑክ ከኤርትራ፣ ከግብፅ እና ከሶማሊያ ሚኒስትሮች ጋር ስለ ቀጣናው ደኅንነት መወያየታቸው ተገለጸ
የአረብ እና የአፍሪካ አገራት ጉዳዮች የአሜሪካ ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቦውሉስ ከኤርትራ፣ ከግብፅ እና ከሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር የአፍሪካ ቀንድን ደኅንነት "በማጠናከር" ዙሪያ መወያየታቸው ተገለጸ። ከሚኒስትሮቹ ጋር የተናጠል ውይይት ያደረጉት የአሜሪካው ከፍተኛ አማካሪ፤ ስለ አፍሪካ ቀንድ "ሰላም፣ ደኅንነት እና መረጋጋት" ማንሳታቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ አስታውቀዋል።
ቀጥታ, ኢራን ከአሸማጋዮች የሰላም እቅድ እንደቀረበላት አስታወቀች
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች አዲስ የሰላም እቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች። አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም እቅድ ማቅረባቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን "ምክክሩን ለማስጀመር እክል" ገጥሞታል መባሉን አስተባበለ
ከአራት ዓመት ሂደት በኋላ ረቡዕ ዕለት የመጨረሻውን ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ያካሄደው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ባለፉት ቀናት ውስጥ "ምክክሩን ለማስጀመር እክል" ገጥሞታል መባሉን አስተባበለ። ባለፉት ሦስት ቀናት ለአራት ሺህዎቹ የጉባኤው ተሳታፊዎች ስለ ሒደቱ ገለጻዎችን መሰጠቱን እና ከነገ ሰኞ አንስቶ "መቶ በመቶ" ወደ ሥራ እንደሚገባ ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።
ግብፅ እና ኤርትራ ቀይ ባሕርን "በሕገ ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚደረግ ሙከራን" አወገዙ
ግብፅ እና ኤርትራ የቀይ ባሕር "ደኅንነት እና አስተዳደር የሚመለከተው የጠረፉን አገራት ብቻ" እንደሆነ ገለጹ። የጠረፉ አካል ያልሆኑ አገራት ቀይ ባሕርን "በሕገ ወጥ መንገድ ለመቆጣጠር የሚደረጉት ሙከራ ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ ነው" ሲሉም አቋማቸውን አንጸባርቀዋል። ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቅርቡ በግብፅ ያደረጉት ጉብኝት “ፍሬያማ” እንደነበርም ተመልክቷል።
በምሥራቅ ጎጃም ታጣቂዎች በ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መኪና ላይ በከፈቱት ተኩስ አምስቱን አቆሰሉ
በአማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን ቢቡኝ ወረዳ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈትነው በሚመለሱ ተማሪዎች ላይ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አምስት ተማሪዎች መጎዳታቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናገሩ።
ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ 'በቁም እስር ላይ' ናቸው?
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለአንድ ዓመት ሲመሩ የነበሩት ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ከሥልጣናቸው ከተወገዱ ወዲህ ስለሚገኙበት ሁኔታ በግልጽ ሳይታወቅ ወራት ተቆጥረዋል። በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ወደ መቀለ ያደረጉትን ጉዞ ተከትሎ ስማቸው የተነሳው ሌተናንት ጄነራል ታደሰ፤ ስላሉበት ሁኔታ ከቅርብ ምንጮች ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ተችሏል።
ኢራን በዮርዳኖስ በፈጸመችው ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች ሲገደሉ አንዱ የደረሰበት አልታወቀም
ኢራን አርብ ዕለት ዮርዳኖስ ውስጥ በፈጸመችው የባለስቲክ ሚሳዔል እና የድሮን ጥቃት፤ ሁለት የአሜሪካ መከላከያ ሠራዊት አባላት እንደተገደሉ እና አንዱ እስካሁን የደረሰበት እንደማይታወቅ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ገለጹ። የአሜሪካ ጦር በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ ኢራን ላይ ሌላ ዙር ጥቃት መፈጸሙን የሠራዊቱ ማዕከላዊ ዕዝ አስታውቋል።
ቢቢሲ አማርኛ በቲክቶክ
አስተማማኝ ዜና እና መረጃን ቅድሚያ ለማግኘት ቢቢሲ አማርኛን ቲክቶክ ላይ ይከተሉ
የዓለም ዋንጫ - 2026
አዳዲስ ታሪክ የሚመዘገብበት 23ኛው የዓለም ዋንጫ ውድድር ሙሉ መረጃን እዚህ ያገኛሉ
የዓለማችን ትልቁ የእግር ኳስ ውድድር የዓለም ዋንጫ በ23ኛ ዙር ውድድር በርካታ አዳዲስ ነገሮች የሚታዩበት ሆኖ ከሰኔ 4 አስከ ሐምሌ 12 ድረስ ይካሄዳል። በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት አገራት ውስጥ የሚካሄደውን የዓለም ዋንጫ ተጎራባቾቹ አሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ ያስተናግዱታል። የውድድር ቦታዎች፣ ቀናት፣ ሰዓታት፣ ውጤቶች፣ የምድብ ድልድል እና ደረጃ እንዲሁም ሌሎች የጨዋታ ዝርዝር መረሃ ግበሮች እዚህ ይቀርባሉ።
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቪድዮዎች
ቪዲዮ, ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስለምርጫ፤ ስለፕሪቶሪያ፤ ስለአርሲ. . . ምን አሉ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተሰናባቹ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ላቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን አንስተዋል። ቢቢሲ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ውስጥ አምስት ዋና ዋና ጉዳዮችን መርጦ አውጥቷል።
የዊግ እና 'ሂውማን ሄር' ከጡት ካንሰር ጋር የሚገናኙ ኬሚካሎች
ፀጉር ላይ የሚቀጠለው ዊግ እና ሂውማን ሄር ከጡት ካንሰር፣ ከሆርሞን መዛባት እንዲሁም በሥነ ተዋልዶ ጤና ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ኬሚካሎችን መያዛቸውን ጥናቶች አሳዩ። ሳይንቲስቶች ዊጎቹ ላይ 50 ጎጂ ኬሚካሎችን አግኝተዋል። እነዚህ ኬሚካሎች ፀጉር ላይ የሚቀጠሉ፣ የሚጠለቁ እንዲሁም የሚሰፉ ዊጎች እና ሂውማን ሄር ላይ ይገኛሉ።
ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር የሚፎካከሩት ዕጩዎች
በዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በኦሮሚያ ክልል ጎማ 2 ምርጫ ክልል ይወዳደራሉ። እርሳቸውን ለማሸነፍ የሌሎች ፓርቲ ዕጩዎችም ይፎካከራሉ። እነዚህ እጩዎች ከአሁን በፊትም ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጋር የተወዳደሩ ናቸው?
ቪዲዮ, የኢትዮጵያ እና የሱዳን መካሰስ እና ፍጥጫ
ለረጅም ጊዜ ወዳጅ ሆነው የቆዩት ጎረቤታሞቹ ኢትዮጵያ እና ሱዳን ግንኙነታቸው ሻክሯል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በይፋ በመውጣት ከመካሰስ አልፈው ወደ ግጭት የሚያመሩ ዛቻዎች እየተሰሙ ነው። ለመሆኑ ሁለቱ ጎረቤታሞችን እዚህ ያደረሳቸው ምንድን ነው?
አነጋጋሪ ጉዳይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ላይ ማሻሻያ ሊኖር እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ በተጀመረው ሀገራዊ ምክክር የመጨረሻ ጉባኤ መክፈቻ ላይ በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ላይ ማሻሻያ ሊኖር እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ። ከአራት ዓመታት በላይ በዋና ዋና አገራዊ ጉዳዮች ላይ አጀንዳ ሲያሰባስብ እና ተወያዮችን ሲያስመርጥ የቆየው ሀገራዊ ምክር ኮሚሽን የመጨረሻውን ምክክር የሚያደርግበትን ጉባኤ ዛሬ ረብዑ ሐምሌ 8 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ ላይ ተጀምሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ "ሰዎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው መሥራት የማይችሉበት ደረጃ" ላይ መደረሱን ኮነኑ
በአማራ ክልል ደብረ ማርቆስ ከተማ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ "ሰዎች በነጻነት ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ሥራ መሥራት ወደማይችሉበት ደረጃ" መደረሱን "አጠያያቂ፣ ጥዩፍ እና የማይገባ" ሲሉ ኮነኑ። በታጣቂዎች ምክንያት የተፈጠሩ የእንቅስቃሴ መገደቦችን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ የሚደረግ የመኪና ጉዞ "በኛ ጥረት መመለስ ይኖርበታል" ሲሉም ተናግረዋል።
የተወሰኑ የአፍሪካ አገራት ለምን ኢትዮጵያ የፈረመችውን የትራምፕ የእርዳታ ስምምነት ውድቅ አደረጉ?
አሜሪካ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋሟን ከዘጋች በኋላ በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቷ በኩል አዲስ ዓለም አቀፍ የጤና ስትራቴጂ ዘርግታለች። በዚህ አሰራር ድጋፍ የሚያገኙ መንግሥታት እንደ የጤና መረጃዎችን ለአሜሪካ ማጋራት ያሉ ኃላፊነቶች ተጥሎባቸዋል። አገራት እና ተቋማት አሰራሩ ላይ ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው። ለምን?
ከጠ/ሚ ዐቢይ የ"አብረን እንሥራ" ጥያቄ የቀረበላቸው ዶ/ር ደሳለኝ ከፖለቲካ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ ከመንግሥታቸው ጋር አብረው እንዲሠሩ ጥሪ ያቀረቡላቸው ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ራሳቸውን ከፖለቲካ ማግለላቸውን አስታወቁ። ደሳለኝ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በእንደራሴነት ያሳለፏቸውን አምስት ዓመታት "አስቸጋሪ እና ፈታኝ" ሲሉ ገልጸዋቸዋል።
"ህወሓትም ጭምር ቀልብ ከገዛ. . . ለመነጋገር ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል" ጠ/ሚ ዐቢይ
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሕዝብ እንደራሴዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "ህወሓትም ጭምር ቀልብ ከገዛ. . . ለመነጋገር ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል" አሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በምርጫ ቦርድ ሕጋዊ እውቅናው የተሰረዘበት ህወሓት የተግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ካስወገደ በኋላ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ፍጥጫ ውስጥ ባለበት ጊዜ ነው።
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቻናልን ይቀላቀሉ
የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን ቀጣናዊ ፖሊሲ የለወጠው የኢራን ጦርነት
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ባላት ግንኙነት የተነሳ የኢራን ዋነኛ ዒላማ ከሆነች በኋላ በቀጣናው አገራት ላይ ያላት መተማመን እየቀነሰች ነው። ለፖለቲካ፣ ለምጣኔ ሃብት እና ሌሎች ፍላጎቷን ለማሟላት ከቀጣናው ውጭ መመልከትን መርጣለች። ለዚህም ከሕንድ፣ ከዩክሬን፣ ከግሪክ፣ ከቆጵሮስ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትስስር እያጠናከረች ነው።
የአሜሪካ እና ኢራን ጦርነትን ያስቆማል የተባለው ስምምነት ምን ምን ይዟል?
የአሜሪካ እና ኢራን ከመግባባት ላይ የደረሱበት ሰነድ ይፋ ሆኗል። ስምምነቱ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲከፈት እንደሚያደርግ እንዲሁም ለወራት የቆየውን ጦርነት ያስቆማል የሚል እምነት አሳድረዋል። ትራምፕ ባለ 14 ነጥቡ ስምምነት "በአፈጻጸም ላይ የተመሠረተ" መሆኑን እና ኢራን ልትጠቀም የምትችለው ስምምነቱን የምታከብር ከሆነ ብቻ ነው ብለዋል። የስምምነቱ ነጥቦች ምን ምን ይዘዋል?
በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የአሜሪካንን ባሕር ኃይል እየፈተኑ ያሉት የኢራን ትናንሽ ጀልባዎች
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራንን ባሕር ኃይል እንዳወደሙ ቢናገሩም፣ ኢራን ትናንሽ ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በሆርሙዝ ወሽመጥ የመርከቦችን እንቅስቃሴን መግታት ችላለች። ስለእነዚህ ውጤታማ የኢራን ፈጣን ወታደራዊ ጀልባዎች ምን እናውያለን?
አሜሪካ እና ኢራን ድል እንደተቀዳጁ እያወጁ ባሉበት ጦርነት አሸናፊው ማን ነው?
አሜሪካ ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ማቆሟን እየተናገረች ነው። በሁለቱ አገራት መካከል የተኩስ አቁም ከተደረገ ከሳምንታት በኋላ ማክሰኞ ዕለት የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ "ኢፒክ ፊውሪ' በማለት የተጠራው ዘመቻ ማብቃቱን ተናግረዋል።በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በተደረገው ጦርነት ማን አሸነፈ?
ከየፈርጁ
በድምጻውያን ጉሮሮ ላይ የቆመው ኤአይ የኢትዮጵያን ሙዚቃ መልክ እንዴት ሊለውጠው ይችላል?
በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) ተገርበው በአዲስ መልክ የተሠሩ ሙዚቃዎች የዩቲዩብ ገፆችን ወርረዋል። የአንጋፋ እና ተወዳጅ ድምጻውያን የሙዚቃ ሥራዎች አማርኛው በተኮላተፈ የኤአይ አንደበት እየተዘፈኑ ነው። አንዳንዶቹ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ዕይታዎች አሏቸው። የአድማጭን ትኩረት የሳቡም ይመስላሉ። ለመሆኑ የዘመኑ የቴክኖሎጂ ልህቀት በተለይ በሙዚቃው ዘርፍ ምን ያሳጣ፣ ምን ያስገኝ ይሆን? የኢትዮጵያን ሙዚቃስ በምን መልኩ ሊለውጠው ይችላል?
ቢቢሲ አማርኛን በዋትስአፕ ላይ ያግኙ
አጃኢብ!
የተመለሱ ጥያቄዎች
ያለባቸው የጤና ችግር ሕክምና እንዲያጠኑ ያደረጋቸው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
በረከት በቀለ፣ ኪምቢፊዳ በሚል ስም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይታወቃል። ወደ ቲክቶክ ብቅ ከማለቱ አስቀድሞ "በስፓይና ቢፊዳ (spina befida) የተያዝኩ ብቸኛው ሰው እኔ ብቻ እንደሆንኩ ይሰማኝ ነበር" ይላል። የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መሥራቹ ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬም ልክ እንደ በረከት ሁሉ ከስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) ጋር ነው የተወለደው። አሁን 33 ዓመት እንደሆነው የሚናገረው ዶ/ር ነቢያት፣ በተወለደ በ22ኛው ቀን የስፓይና ቢፊዳ የቀዶ ሕክምና ተደርጎለታል። ሁለቱም ወጣቶች ከራሳቸው ህመም ተነስተው ሕክምና ለማጥናት መወሰናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያዊ እና ኬንያዊ አትሌቶች ማራቶንን ከሁለት ሰዓት ባነሰ ጊዜ እንዲጨርሱ ያስቻላቸው ምስጢር ምንድን ነው?
ትናንት እሁድ በለንደን የተካሄደው የማራቶን ውድድር ኬንያዊው ሳባስቲያን ሳዌ እና ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻ ከሁለት ሰዓት በታች ተከታትለው በመግባት ዓለምን አስደምመዋል።
የኢንተርኔት ዳታን በመቆጠብ የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽን በቀላሉ ማንበብ ይፈልጋሉ?
የቢቢሲ አማርኛን ድረ ገጽ በቀላሉ በመክፈት ዜና እና ታሪኮችን በጽሑፍ ብቻ ያንብቡ!















































































































