ፎቶ፡ የአሸንዳ በዓል ከሦስት ዓመታት በኋላ በመቀለ በድምቀት ተከበረ

የተለያዩ መጠሪያዎች ያሉት ይህ በዓል በትግራይ እና አማራ ክልሎች በወጣት ሴቶች ዘንድ በድምቀት ይከበራል።
ታትሟል

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በሰሜን ኢትዮጵያው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት ለሦስት ዓመታት ሳይከበር የቆየው የአሸንዳ በዓል በትግራይ ክልል መዲና መቀለ በድምቀት ተከበረ።

የተለያዩ መጠሪያዎች ያሉት ይህ በዓል ከማክሰኞ ነሐሴ 16/2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች መከበር ጀምሯል።

ከሦስት ዓመታት በኋላ በትግራይ መዲና መቀለ የበዓሉን አካባበር የሚያሳዩ የሚያሳዩ ምስሎችን እዚህ ይመልከቱ።

ይህ በዓል በዋግ ኸምራ ሻደይ፣ በላስታ ላሊባላና ጎንደር አሸንድዬ እንዲሁም በራያ ቆቦ ሶለል እንዲሁም በትግራይ አሸንዳ፣ አይኒዋሪ እና ማርያ በሚል ይጠራል።
የምስሉ መግለጫ, የተለያዩ መጠሪያዎች ያሉት ይህ በዓል በትግራይ እና በአማራ ክልሎች በወጣት ሴቶች ዘንድ በድምቀት ይከበራል።
 ይህ በዓል በዋግ ኸምራ ሻደይ፣ በላስታ ላሊባላና ጎንደር አሸንድዬ እንዲሁም በራያ ቆቦ ሶለል እንዲሁም በትግራይ አሸንዳ፣ አይኒዋሪ እና ማርያ በሚል ይጠራል።
የምስሉ መግለጫ, ይህ በዓል በዋግ ኸምራ ሻደይ፣ በላስታ ላሊባላ እና በጎንደር አሸንድዬ እንዲሁም በራያ ቆቦ ሶለል እንዲሁም በትግራይ አሸንዳ፣ አይኒዋሪ እና ማርያ በሚል ይጠራል።
በሰሜን ኢትዮጵያው የተካሄደው ጦርነት በተለይ በሴቶች እና ሕንጻና ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ አድርሷል።
የምስሉ መግለጫ, በሰሜን ኢትዮጵያው የተካሄደው ጦርነት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ሕይወት አሳጥቷል፤ አካል አጉድሏል።
ይህ በዓል ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶች አሉት። የበዓሏን አመጣጥ ከክርስትና እምነት ጋር የሚያይዙት በዓሉ የሚከበረው የፍልሰታ ፆም ማብቂያ ላይ ነው ይላሉ።
የምስሉ መግለጫ, ይህ በዓል ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ትውፊቶች አሉት፤ የበዓሉን አመጣጥ ከክርስትና እምነት ጋር የሚያይዙት በዓሉ የሚከበረው የፍልሰታ ፆም ማብቂያ ላይ ነው ይላሉ።
በዓሉን ከአዲስ ዓመት መቀበያ ወቅት ጋር ከመከበሩ አንጻር የበዓሉ መነሻ አዲስ ዓመት ነው የሚሉም አሉ።
የምስሉ መግለጫ, በዓሉን ከአዲስ ዓመት መቀበያ ወቅት ጋር ከመከበሩ አንጻር የበዓሉ መነሻ አዲስ ዓመት መምጣት ጋር ይገናኛል ይላሉ።
የበዓሉ ታዳሚዎች
የምስሉ መግለጫ, ትናንት የተጀመረው የአሸንዳ በዓል በቀጣይ ቀናት በመከበር ይቀጥላል።
ይህን በዓል ልጃገረዶች ድምቀት ያከብሩታል።
የምስሉ መግለጫ, ይህን በዓል ልጃገረዶች ድምቀት ያከብሩታል።