የዝውውር ጭምጭምታ፡ ዛሃ፣ ቤንቴኬ፣ ባብል፣ ጎትዘ፣ ትራዎሬ፣ ቪዳል እና ሌሎች

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የጄነዋሪ ወር የተጫዋቾች የዝውውር ጭምጭምታ፡ ዛሃ፣ ቤንቴኬ፣ ባብል፣ ጎትዘ፣ ትራዎሬ፣ ቪዳል እና ሌሎችም
ቼልሲ የክርስታል ፓላሱን እና የአይቮሪ ኮስት የፊት መስመር ተጫዋቹን ዊልፍሬድ ዛሃን ለማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ኤክስፕረስ አስነብቧል።
ይሁን እንጂ ቼልሲዎች፤ ክሪስታል ፓላሶች የጠየቁትን 80 ሚሊዮን ፓዎንድ ለመክፈል ዝግጁ አይመስሉም።

ማንችስተር ሲቲ የዎልቭሱን ፈርጣማ አጥቂ አዳማ ትራዎሬን ለማስፈረም ፍላጎት አላቸው። ዎልቭስ በዘንድሮ የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች በሲቲዎች ላይ የበላይነትን ሲቀዳጁ የ23 ዓመቱ አዳማ ትራዎሬ ተጽእኖ ፈጣሪ ተጫዋች ነበር። ይህን የዘገበው ማንችስተር ኢቪንንግ ኒውስ ነው።

የባርሴሎና እና የቺሊ አማካይ አርቱሮ ቪዳል ወኪል ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር እንደሚነጋገር የዘገበው ሚረር ነው። እንደዘገባው ከሆነ፤ ቪዳል በጃንዋሪ የዝውውር መስኮት ወደ ማንችስተር ሊያቀና ይችላል።

አስቶን ቪላዎች የክሪስታል ፓላሱን ክሪስቲያን ቤንቴኬን ለማስፈረም ንገግር ላይ መሆናቸውን የዘገበው ቴሌግራፍ ነው።
አስቶን ቪላ የቀድሞ የሊቨርፑል የአሁኑን የኤሲ ሚላን ግብ ጠባቂ ፔፔ ሬይናን እንዲያስፈርሙ ጥያቄ እንደቀረበላቸው ደግሞ ሜይል ዘግቧል።

ጀርመን የ2014ቱን የዓለም ዋንጫ ስታነሳ ማሸነፊያ ጎሉን ያስቆጠረው ማሪዮ ጎትዘ የውድድር ዓመቱ ሲጠናቀቅ በነጻ ዝውውር ከቦሪሲያ ዶርትመንድ እንደሚለያይ የዘገበው ሚረር ነው። በዘገባው ጎትዘ ወዴት ሊያቀና እንደሚችል አልተጠቀሰም።

ኒውካስትል ዩናይድ የቀድሞውን የሊቨርፑል አማካይ ባብል ከጋላታሳራይ የማስፈረም ፍላጎት እንዳላቸው ኤክስፕረስ ዘግቧል። የቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ ባብልን የማሰናበት ፍላጎት እንዳለው እና አያክስም ፍላጎት እንዳለው በዘገባው ተጠቅሷል።

ዘጋርዲያን እንደዘገበው ከሆነ ዌስት ሃም የቤኔፊካውን አማካይ ጌድስን ፈርናንዴስ ለማስፈረም ሲያደርግ የነበረው ጥረት አልተሳካም።

ኤቨርተን የጁቬንቱሱን ፈረንሳይዊ አማካይ አድሪያን ራቢዮት የዘንድሮ የውድድር ዓመት እስኪጠናቀቅ ድረስ በውሰት ማዘዋወር እንደሚፈልግ የዘገበው ስፖርት ዊትነስ ነው።

ከብራይተን ወደ ሊድስ ዩናይትድ በውሰት የሄደውን የ22 ዓመት ተከላከይ ቤን ዋይት ለማስፈረም ፍላጎት ካላቸው ክለቦች መካከል ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ቶተነሃም ተጠቃሽ መሆናቸውን ያስነበበው ስካይ ስፖርት ነው።

መድፈኞቹ በጃንዋሪ የዝውውር መስኮት ቋሚ ተጫዋች የማስፈረማቸው እድል የተመናመነ መሆኑን፤ ይሁን እንጂ በውሰት ግን ተጫዋች ከሌላ ክለብ ሊያስፈርሙ እንደሚችሉ ጎል አስነብቧል።













