ለቀናት የሚዘልቀው የኢራን የቀድሞ ጠቅላይ መሪ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተጀመረ
የኢራን የቀድሞ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት እና ሕዝባዊ ሐዘን ተጀምሯል።
ከአራት ወራት በፊት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መሰንዘር ሲጀምሩ ነበር ኻሜኒ የተገደሉት።
ቀብራቸው የሚፈጸመው በትውልድ ከተማቸው ማሻሀድ የፊታችን ሐሙስ ይሆናል። እስከዚያም አስከሬናቸው በቴህራን በሚገኘው ግራንድ ሞሳላ መስጊድ ይቆያል።
የኢራን ባለሥልጣናት “የዘመኑ የቀብር ሥነ ሥርዓት” ሲሉ ክንውኑን የገለጹት ሲሆን፤ ከ12 እስከ 20 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች እንደሚገኙ ተገልጿል።
ኢራን እና አሜሪካ የመግባቢያ ሰነድ ከተፈራረሙ በኋላ ለተወሰኑ ቀናት የተኩስ ልውውጦች ቢደረጉም፤ ወደ ድርድር ለመመለስ ተስማምተዋል።
ትናንት አርብ የኻሜኒ የሬሳ ሳጥን በኢራን ሰንደቅ ዓላማ ተሸፍኖ መስጊድ ውስጥ ታይቷል።
በሥፍራው ከተገኙ መካከል የኢራን ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዤሽኪያን ይገኙበታል።
አሜሪካ እና ኢራንን ያደራደረችው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሻባዝ ሻሪፍ፣ የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዝዳንት ዲሚትሪ ማድቬዴቭ እና የአፍጋኒስታኑ ታሊባን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚር ካሀን ሙታቂም ተገኝተዋል።