ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
የሞሮኮን ንጉሥ የተሳደበው አራት ዓመት ተፈረደበት
ታትሟል
ዝነኛ የሆነው ሞሮኮያዊ ዩቲዩበር የአገሪቱን ንጉሥ በመሳደቡ የአራት ዓመት ጽኑ እስራት እና የ4ሺህ ዶላር መቀጮ ተጣለበት።
ሞሐመድ ሴካኪ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ነበር የንጉሥ ሞሐመድን ንግግር በመተቸቱ እና ሕዝቡን 'አጋሰስ' ብሎ በመስደቡ በቁጥጥር ሥር የዋለው።
ሞሐመድ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ይግባኝ እንደሚል ተነግሯል።
በተመሳሳይ መልኩ ጋዜጠኛ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆነው ኦማር ራዲ፤ የፍርድ ቤት ዳኛን ተሳድባል ተብሎ በቁጥጥር ሥር ውሏል።
የመብት ተሟጋቾች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሞሮኮ የዜጎች ነጻነት ላይ ከፍተኛ ገደብ እየተጣለ ነው ይላሉ።
ንጉስ ሞሐመድ ስድስተኛ ከአረብ አብዮት በኋላ ያላቸውን ስልጣን ተመርጦ ስልጣን ለያዘው መንግሥት ያጋሩ ቢሆንም አሁንም ድረስ ወሳኝ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጡት እሳቸው ናቸው እየተባሉ ይተቻሉ።