እስራኤል በጋዛ ላይ የምታካሂደውን ዘመቻ አጠንክራ እንደምትቀጥል አስታወቀች

የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት የአገራቸው ሠራዊት በጦርነቱ የሚያካሂደው ዘመቻ ያለበት ደረጃ “መቀየሩን” በመግለጽ፣ “ተጨማሪ መረጃ አስኪሰጥ ድረስ” ዘመቻው ይቀጥላል ብለዋል። አርብ ምሽት ሠራዊቱ በወሰደው እርምጃ “የጋዛ ምድር ተንቀጥቅጣለች” በማለት የመከላከያ ሚኒስትሩ ለአንድ ቴሌዥን ጣቢያ ተናግረዋል።

የቀጥታ ሽፋን

  1. ባለፉት 24 ሰዓታት ጋዛ ውስጥ 436 ሰዎች ተገድለዋል፡ የጋዛ ጤና ሚኒስቴር

    ጋዛ ከአየር ድብደባ በኋላ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ጋዛ ውስጥ የሚገኘው የጤና ሚኒስቴር አንዳስታወቀው የእስራኤል የአየር ጥቃት በቀጠለበት ሁኔታ በአንድ ቀን ውስጥ 436 ሰዎች ተገድለዋል።

    ሁለት ሳምንት ባለፈው የአየር ጥቃት ጋዛ ውስጥ የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ5,000 ማለፉ ተገልጿል።

    በጋዛ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር በአሁኑ ወቅት 5,087 የደረሰ ሲሆን፣ ትናንት ብቻ የሟቾች ቁጥር በ436 ጨምሯል።

    ከተገደሉትመካከል 2,055 ሕጻናት፣ 1,119 ሴቶች፣ 217አረጋውያን እንደሚገኙበትተገልጿል።

    በአስራኤል የአየር ጥቃት ከተገደሉት ሰዎች በተጨማሪ ከ15,273 በላይ ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

    በጋዛ የሚገኘው የጤና ሚኒስቴር ግዛቲቱን በሚቆጣጠረው እና ከእስራኤል ጋር ግጭት ውስጥ በገባው በሐማስ ቁጥጥር ስር የሚገኝ ነው።

    እስራኤል በጋዛ ላይ የምትፈጽመው የቦምብ ድብደባ ትናንትና ቀን እና ሌሊቱንም የቀጠለ ሲሆን፣ ከጋዛ የወጡ ፎቶዎች የወደሙ ሕንጻዎችን እና በጥቃቱ የተጎዱ ሰዎች ከሆስፒታሎች አቅራቢያ ባሉ መንገዶች ላይ ተኝተው አሳይተዋል።

    ዛሬ ጠዋት የእስራኤል ጦር ሠራዊት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ጋዛ ውስጥ የሚገኙ 320 ዒላማዎችን መምታቱን ገልጿል። በዚህም የሐማስ ተዋጊዎች የሚገኙባቸው ዋሻዎች እና የቡድኑ የቅኝት ማማዎች ወድመዋል።

    የአስራኤል ሠራዊት በሲቪሎች ላይ የደረሰን ጉዳት በተመለከተ በሰጠው ምላሽ፣ ዓለም አቀፍ ሕግን በመከተል “በሲቪሎች ላይ የሚደርስን ጉዳት ለማስወገድ አስፈላጊው ቅድመ ጥንቃቄ ይደረጋል” ብሏል።

  2. እስራኤል በጋዛ ስለምታደርገው ዘመቻ እስካሁን የምናውቀው

    ባለፉት 24 ሰዓታት የእስራኤል ወታደሮች ወደ ጋዛ ወረራ መፈጸማቸው ተገልጿል። እስካሁን የምናውቃቸው ዋና ዋና ነጥቦች ቀጣዮቹ ናቸው።

    እሑድ:

    • እሑድ የእስራኤል ወታደሮች በጋዛ ሰርጥ ምዕራባዊ ክፍል ገብተው ታጋቾችን እንደፈለጉ፣ አካባቢውን ከአሸባሪዎች እና ከመሣሪያ ለማጽዳት እንደሞከሩም እስራኤል አስታውቃለች።

    • የእስራኤል መከላከያ ኃይል እንዳለው ሚሳኤሎች በሐማስ ተተኩሰውባቸዋል። አንድ የእስራኤል ወታደር እንደተገደለ እና ሦስት ወታደሮች እንደቆሰሉ ተገልጿል።

    • የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ እንዳለው ይህ የተከሰተው በደቡባዊ ጋዛ ኻን ዩኒስ ነው። ይህ ከተማ ፍልስጤማውያን ለደኅንነታቸው ሲሉ ትተውት እንዲወጡ የተጠየቀ ነው። የእስራኤል ወታደሮች ወደ “በበርካታ ሜትሮች” ጥሰው እንደገቡም ተገልጿል።

    • የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ እንዳለው “ከወራሪው ኃይል ጋር ተዋግቷል።” ሁለት ቡልዶዘሮች እና ታንክ እንዳወደሙም ገልጸዋል። እስራኤላዊ ወታደሮች መኪናቸውን ትተው በእግራቸው ወደ ምሥራቃዊ አቅጣጫ ሸሽተዋል።

    ሰኞ:

    • የእስራኤል መከላከያ ኃይል ቃል አቀባይ ዳንኤል ሐጋሪ እንዳሉት፣ እስራኤል በአንድ ምሽት ብዙ ወረር በጋዛ ላይ ፈጽማለች።

    • ቃል አቀባዩ አክለውም “ምሽት ላይ ዘመቻው ሲካሄድ በታንክ እና በእግረኞች ነው። አሸባሪዎችን የገደሉት እነዚህ ዘመቻዎች ለቀጣይ የጦርነቱ ክፍል የተደረገ ዝግጅትን ኢላማ አድርገዋል። የታገቱ ሰዎችን ለማግኘት እና የደኅንነት መረጃ ለማግኘትም ጠልቀን ወደ ውስጥ ገብተዋል” ብለዋል።

    ይህ የእስራኤል ወታደሮች ወደ ጋዛ ዘልቀው የገቡበት የመጀመሪያው ጊዜ አይደለም። በግጭቱ የመጀመሪያው ሳምንት እስራኤል ወታደሮቿ እና ታንኮች ወደ ጋዛ ሰርጥ ሐማስን ለመዋጋት እና ወደ እስራኤል የሚወነጨፉ ሚሳኤሎችን ለማግኘት እንደገቡ ገልጻለች።

  3. በጋዛ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ5 ሺህ አለፈ

    በጋዛ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ5,000 ማለፉን የፍልስጤማ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

    በጋዛ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 5,087የደረሰ ሲሆን፣ ከትላንትናው የሟቾች ቁጥር በ436ጨምሯል።

    ከተገደሉት መካከል 2,055ሕጻናት፣ 1,119ሴቶች፣ 217አረጋውያን እንደሚገኙበት ተገልጿል።

    ከ15,273በላይ ሰዎች ተጎድተዋል።

  4. ሕይወት በጋዛ፡ ከቤት ተፈናቅሎ መጠለያ ፍለጋ መንከራተት

  5. በጋዛ በቅርቡ ከተፈጸሙ የአየር ጥቃቶች የተገኙ ምስሎች

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ እያደረገችው ያለው ወታደራዊ ዘመቻ ወራት ሊፈጅ እንደሚችል አስታውቃ የአየር ጥቃቷንም አጠናክራ ቀጥላለች።

    በነዚህ ጥቃቶች ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ህጻናት እና ሴቶች መሆናቸውን ከጋዛ የጤና ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።

    በአጠቃላይም 4 ሺህ 651 ፍልስጥኤማውያን ተገድለዋል።

    እሁድ ምሽቱን በሙሉ እስራኤል በፈጸመቻቸው ጥቃቶች በርካታ ህንጻዎች መውደማቸውን እና መቁሰላቸውንም ከስፍራው የተገኙ ምስሎች ያሳያሉ።

    ከተለያዩ የዜና ኤጀንሲዎች የተገኙት እነዚህ ምስሎች የሚረብሽ ይዘት አላቸው።

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

  6. እስራኤል በጋዛ ላይ የምታካሂደው 'ወታደራዊ ዘመቻ' ወራት ሊወስድ እንደሚችል አስታወቀች

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት በጋዛ የሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ "አንድ፣ ሁለት ወይም ሶስት ወራት ሊወስድ እንደሚችል አስታወቁ።

    ነገር ግን በመጨረሻም ሐማስ መኖሩ ያከትማል" ሲሉም በእስራኤል የአየር ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

    "ወታደራዊ ዘመቻውን በተመለከተ የእስራኤልን መከላከያ ሰራዊት ምንም ነገር አያቆመውም" ሲሉም ተናግረዋል።

    "ይህ በጋዛ ላይ የምናደርገው ዘመቻ የመጨረሻችን ሊሆን ይገባል ምክንያቱም ከዚህ በኋላ ሐማስ አይኖርም" ሲሉም ተደምጠዋል።

    ሚኒስትሩ የእስራኤል ኃይል በጋዛ ላይ እያደረሰ ላለው ጥቃት አድናቆታቸውን ገልጸው ሲጠበቅ የነበረውም የእግረኛ ጦር በቅርቡ ወደ ጋዛ እንደሚገባ ናግረዋል።

    እስራኤል ላለፉት ሁለት ሳምንታት ቀን ተሌት ጋዛን በቦምብ በመደብደብ ላይ የምትገኝ ሲሆን በዚህም 4 ሺህ 651 ፍልስጥኤማውያን ተገድለዋል።

    መቼ ሊሆን እንደሚችል ግን ቀኑን አልጠቀሱም።

    የሆላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩት እና ፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት እስራኤልን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።

  7. ሆስፒታሎቿ በቁስለኞች እና በአስከሬን በተጨናነቁባት ጋዛ የአየር ጥቃቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል

  8. በጋዛ- እስራኤል የተከሰቱ ዋና ዋና ጉዳዮች

    ወደ ጋዛ የሚገባው እርዳታ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ሌት ተቀን የምትፈጽመው የአየር ጥቃት ለ16ኛ ቀን ቀጥሏል። እሁድ አመሻሽ ላይ የተከሰቱ ዋና ዋና ጉዳዮችን እንመልከት፦

    • እርዳታ የጫኑ 14 ተሽከርካሪዎች በከበባ ላይ ባለችው ጋዛ ሰርጥ እንዲገቡ ፍቃድ አግኝተዋል። ግጭቱ ከተጀመረ በኋላ እርዳታ ሲገባ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ ዋና ጸሐፊ ማርቲን ግሪፍትስ በግዛቲቱ ላሉ ነዋሪዎች "የተስፋ ጭላንጭል" የፈነጠቀ ነው ብለውታል።
    • "በቀን እርዳታ የጫኑ ጥቂት የጭነት መኪናዎችን እንዲገቡ መፍቀድ በቂ አይደለም" ሲሉ የኦክስፋም የሰብዓዊ እርዳታ ኃላፊ ማግኑስ ኮርፊሰን ለቢቢሲ ተናግረዋል። የረድዔት ድርጅቶቹ ወደ ጋዛ "ያልተገደበ እርዳታ እንዲያደርሱ" ሊፈቀድላቸውም ይገባል ሲሉም አክለዋል።
    • የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ናታንያሁን ካናገሩ በኋላ መሪዎቹ "ለተቸገሩ ፍልስጥኤማውያን እርዳታ ባልተቋረጠ መልኩ እንዲገባ" ተስማምተናል ብለዋል።
    • የእስራኤል ቀኝ አክራሪ የደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን ጊቨር ሐማስ በእጁ ያሉ ታጋቾችን በሙሉ ለመልቀቅ ካልተስማማ ለጋዛ "ቀጣይ እርዳታ" ዋስትና ሊሰጥ አይገባም ሲሉ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
    • የምዕራባውያኑ አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን እና ጣልያን መሪዎች እስራኤል "ራሷን ከሽብርተኝነት የመከላከል መብት" አላት በማለት በጋራ ድጋፋቸውን በድጋሜ ገልጸዋል። ሆኖም "ለአለም አቀፉ የሰብዓዊ ህግጋት ተገዢ እንድትሆን" ጥሪ አቅርበዋል።
    • የኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩቴ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሚቀጥለው ሳምንት እስራኤልን እንደሚጎበኙ አስታውቀዋል።
    • ጸረ ታንክ ሚሳኤሎችን እና ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ለማስወንጨፍ የታቀደበትን ሁለት የሄዝቦላህ የጦር ማዕከላት መምታቱን የእስራኤል መከላከያ አስታውቋል።
    • በመቶዎች የሚቆጠሩ እሰራኤላውያን በለንደን ታርፋልጋር አደባባይ ለሰልፍ የወጡ ሲሆን በጋዛ የታገቱ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።
  9. የአሜሪካዋ ዲትሮይት ከተማ ምኩራብ ኃላፊ ተገድለው ተጣሉ

  10. እስራኤል የጋዛን ጦርነት ካላቆመች ቀጠናው ከቁጥጥር ውጭ ሊወጣ እንደሚችል ኢራን አስጠነቀቀች

  11. በጋዛ ከተገደሉት የህጻናቱ ቁጥር ከፍተኛውን ይይዛል- የጋዛ የጤና ሚኒስቴር

    በጋዛ ላይ የደረሰው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በጋዛ ሰርጥ ከተገደሉት የህጻናት ቁጥር ከፍተኛውን እንደሚይዝ የጋዛ የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

    በባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከተገደሉት 4 ሺህ 651 ፍልስጥኤማውያን መካከል 1 ሺህ 873 ህጻናት እንዲሁም 1 ሺህ 101 ደግሞ ሴቶች መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

    በአጠቃላይም 4 ሺህ 651 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸውን እንዲሁም 14 ሺህ 245 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውንም አክሏል።

    በሐማስ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የጤና ሚኒስቴር ከተገደሉት ውስጥ 839 የሚሆኑት በእስራኤል አስገዳጅ ትዕዛዝ ከሰሜን ጋዛ እንዲሸሹ የተነገራቸው መሆናቸውንም አስታውቋል።

    ከሁለት ሳምንታት በፊት ሐማስ በወሰደው ያልተጠበቀ ወታደራዊ እርምጃ 1ሺህ 400 ሰዎች በእስራኤል ተገድለዋል።

    እስራኤል ላለፉት ሁለት ሳምንታት ቀን ተሌት ጋዛን በቦምብ በመደብደብ ላይ የምትገኝ በቅርቡም እግረኛ ጦሯን እንደምታስገባም እየተጠበቀ ይገኛል።

  12. ከሐማስ እና ከሒዝቦላህ ማን ጠንካራ ጦር አለው? አሜሪካ እና ኢራንስ ወደ ግጭቱ ይገቡ ይሆን?

  13. ፀረ - ሴማዊነት ምንድን ነው? ፀረ - ጽዮናዊነትስ?

  14. በጋዛ በቅርቡ ከተፈጸመው የአየር ጥቃት የተገኙ ፎቶዎች

    በጋዛ ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ በአንድ ሌሊት በፈጸመችው ጥቃት 55 ሰዎች መገደላቸውን ሐማስ አስታውቋል።

    እስራኤል በጋዛ ላይ የምትፈጽመው የማያባራ ጥቃት በቀጠለበት ወቅት ህንጻዎች መውደማቸውን፣ ነዋሪዎች ከወደሙ ህንጻዎች ፍርስራሽ ስር ያሉትን ለማዳን እየታገሉ የሚያሳዩ ምስሎችም ወጥተዋል።

    በሙሉ ከበባ ላይ ባለችው ጋዛ የምግብ እጥረትና ነዳጅ ያጋጠመ ሲሆን በርካቶችም ዳቦ ለመግዛት ከዳቦ ቤቶች ውጭ በወረፋዎች ላይ ታይተዋል።

    እስራኤል በጋዛ ላይ ጠንከር ያለ የአየር ጥቃት እንደምትፈጽም አስጠንቅቃለች።

    በሰሜን ጋዛ የሚገኙ ፍልስጥኤማውያንም በፍጥነት ወደ ደቡብ ጋዛ በመሸሽ ህይወታቸውን እንዲያድኑም የእስራኤል መከላከያ ኃይል በድጋሚ አሳስቧል። ጦሩ በቀጣይ በሚወስደው እርምጃ ሐማስን ከምድረ ገጽ እንደሚያጠፋም ዝቷል።

    በጋዛ ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    በጋዛ ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, EPA

    በጋዛ ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, EPA

  15. ዓለም አቀፉ የቀይ ጨረቃ ድርጅት የጋዛ ሆስፒታሎች ነዳጅ ካላገኙ እንደሚዘጉ አስጠነቀቀ

    ወደ ጋዛ የገባው እርዳታ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ዓለም አቀፉ የቀይ ጨረቃ ድርጅት የጤና ማዕከላት አገልግሎታቸውን እንዲሰጡ ነዳጅ ወደ ጋዛ መግባት እንዳለበት አስጠነቀቀ።

    ትናንትና በራፋህ ድንበር በኩል ወደ ጋዛ የገባው የሰብዓዊ እርዳታ ነዳጅ አለማካተቱንም ተከትሎ ነው ተቋሙ ማሳሰቢያውን ያወጣው።

    የፍልስጥኤም የቀይ ጨረቃ ቢሮ ሰራተኛ የሆኑት ኔባል ፋስካህ "ሰብዓዊ እርዳታው ሆስፒታሎች አገልግሎት ማስቀጠል የሚያስችላቸውን መሰረታዊ የሆነውን ነዳጅ አልያዘም" ሲሉም ለቢቢሲ ተናግረዋል።

    "ነዳጅ ካለቀብን ሆስፒታሎች ይዘጋሉ" ያሉት ኔባል የጋዛ ሰርጥ ሁኔታ "ልብን የሚሰብር ነው" ሲሉም ገልጸውታል።

    20 የሰብአዊ እርዳታ ምግብና ቁሳቁስ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች በራፋህ ድንበር በትናንትናው ዕለት አልፈዋል።

    የጋዛ ነዋሪዎች ሰብአዊ እርዳታ ሲቀርብላቸው ከጦርነቱ ወዲህ የትናንቱ ለመጀመርያ ጊዜ ነው። ቅዳሜ እለት ወደ ጋዛ የገባው የእርዳታ አቅርቦት መድኃኒት፣ ምግብ፣ ውሃ እና የሬሳ ሳጥን ያካተተ ቢሆንም እስራኤል ነዳጅ ድንበር ተሻግሮ እንዲገባ አልፈቀደችም።

    እስራኤል ጋዛ ሰርጥን ሙሉ በሙሉ በመዝጋት ከበባ እንዲደረግ ያዘዘች ሲሆን፣ በጋዛ 'ኤሌክትሪክ፣ ምግብ፣ ነዳጅ መግባት ተከልክሏል።

  16. በጋዛ በአንድ ሌሊት በተፈጸመ የአየር ጥቃት 55 ሰዎች መገደላቸውን ሐማስ አስታወቀ

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ የፈጸመችው የአየር ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ትናንት ሌሊት በፈጸመችው የአየር ጥቃት ቢያንስ 55 ፍልስጥኤማውያን መገደላቸውን ሐማስ አስታወቀ።

    በዚህ የአየር ጥቃት 30 መኖሪያ ቤቶች መውደማቸውንም ኤኤፍፒ ሐማስን ዋቢ አድርጓል።

    እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ የምትፈጽመውን የአየር ጥቃት አጠናክራ እንደምትቀጥል እና የእግረኛ ጦሯንም ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆኗን አስታውቃለች።

    በሰሜን ጋዛ የሚኖሩ ፍልስጥኤማውያንም ሙሉ በሙሉ ወጥተው ወደ ደቡባዊ ጋዛ እንዲሄዱም ጦሩ እያስጠነቀቀ ይገኛል።

    የእስራኤል ጦር ቃለ አቀባይ ዳንኤል ሃጋሪ ጥቃቱ በጋዛ ድንበር አካባቢ ለተከማቸው የእስራኤል ጦር ላይ የደቀነውን አደጋም ለመቀነስ ይረዳል ብለዋል።

    ከጋዛ በተጨማሪ እስራኤል በተቆጣጠረችው ዌስት ባንክ ላይ የአየር ጥቃት ፈጽማለች።

    ጦሩ የ"አሸባሪዎች ማዘዣ ማዕከል" እንደሆነ የገለጸውን በጄኒን የስደተኞች መጠለያ የሚገኘው መስጂድን ኢላማ አድርጌያለሁ ብሏል።

  17. በዩኬ እና አሜሪካ ለፍልስጥኤም ድጋፋቸውን ለመግለጽ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አደባባይ ወጡ

    በዩኬ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የምስሉ መግለጫ, በዩኬ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    በአሜሪካ እና በዩናይትድ ኪንግደም ከተሞች ፍልስጥኤምን የሚደግፉ ሰልፎች ተካሄዱ።

    በሁለቱም አገራት ድጋፋቸውን ለፍልስጥኤም ለመግለጽ በአደባባይ የወጡ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች "ነጻ ፍልስጥኤም ሲሉም" ተደምጠዋል።

    የፍልስጥኤምንም ሰንደቅ ዓላማ ሲያውለበልቡ ታይተዋል።

    ለሁለተኛ ሳምንት በለንደን በተደረገው የፍልስጥኤም የድጋፍ ሰልፍ እስከ 100 ሺዎች ተሳትፈውበታል።

    የምዕራቡ አገራት መንግሥታት ለእስራኤል እያሳዩት ያለውን ድጋፍም ተቃውመዋል።

    በዩኬ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የምስሉ መግለጫ, በዩኬ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ
    በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ
    በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ
    በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, በአሜሪካ ለፍልስጥኤም የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ
  18. የተመድ ኤጀንሲዎች በጋዛ ሰብዓዊ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ጥሪ አቀረቡ

  19. ሐማስ፣ እስራኤል እና ምዕራባውያንን የተቹት የሳዑዲው ልዑል ለምን አነጋጋሪ ሆኑ?

  20. 90 ሰዎችን ያስጠለለው ባለአራት መኝታው የጋዛ መኖሪያ ቤት