
የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የምስሉ መግለጫ, ማርቲን ግሪፊትስየመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ በአስራኤል እና በድርጀቱ መካከል ያለው ውዝግብ እየተባባሰ
ባለበት ጊዜ፣ እስራኤል ለተመድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ቪዛ ከለከለች።
የድርጅቱ የሰብአዊ ጉዳዮች ዋና ፀሐፊ የሆኑት ማርቲን ግሪፊትስ ወደ እስራኤል እንዳይገቡ ቪዛ ተከልክለዋል። በመንግሥታቱ
ድርጅት የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት ጊላድ ኤርዳን እርምጃው ተመድን ለመቅጣት መሆኑን ተናግረዋል።
ማክሰኞ ምሽት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በእስራኤል እና በጋዛ ጦርነት ላይ ለመወያየት በተቀመጠው ስብሰባ ምክንያት ነበር በድርጅቱ እና በቴል አቪቭ መካከል ውዝግብ ተፈጠሯል።
የድርጅቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ከ1400 በላይ ሰዎች የተገደሉበት የሐማስ ጥቃት “ዝም ተብሎ የተፈጠረ” አይደለም ሲሉ እስራኤል “ለ56 ዓመታት በፍልስጥኤም ያደረገችውን ወረራ” በማመልከት ተናግረዋል።
አስተያየቱን ተከትሎ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤሊ ኮኸን “ለእንዲህ ዓይነቱ እልቂት ምንም ምክንያት መቅረብ የለበትም” ሲሉ ቁጣ አዘል ምላሽ ሰጥተዋል።

የፎቶው ባለመብት, EPA
የምስሉ መግለጫ, አንቶኒዮ ጉተሬዝ"በየትኛው ዓለም ነው የምትኖረው?" ሲሉ ለጉተሬዝ ጥያቄ አቅርበዋል። ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኃላፊ ጋር የሚያደርጉትን ስብሰባ እንደሰረዙም አክለው ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የእስራኤል አምባሳደር የሆኑት ጊላድ ኤርዳን “የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ለመምራት ብቁ አይደሉም” በማለት ጉተሬዝ ሥልጣን እንዲለቁ ጠይቀዋል።
ጉተሬዝ ኋላ ላይ በኤክስ (ትዊተር) ገጻቸው “የፍልስጥኤማውያን ሕመም ሐማስ ላደረሰው አሰቃቂ ጥቃት ምክንያት ሊሆን አይችልም፤ እንዲሁም በፍልስጥኤም ሕዝብ ላይ የሚፈጸመውን የጅምላ ቅጣትን ትክክል አያደርገውመ” ብለዋል።
አሁን ደግሞ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባለሥልጣናት ቪዛ እንደምትከለክል እስራኤል አስታውቃለች።
ለእስራኤሉ ሬዲዮ ሃሳባቸውን የሰጡት ኤርዳን የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ምክትል ዋና ፀሐፊ ማርቲን ግሪፊትስ ቪዛ መከልከላቸውን ተናግረዋል። "እነሱን የምናስተምርበት ጊዜ ደርሷል" ሲሉ ኤርዳን ገልጸዋል።