ሆንግ ኮንግ ለ7.4 ሚሊየን ነዋሪዎቿ በነፃ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ልታደርግ እንደሆነ አስታወቀች። መሪዋ ካሬ ላም እንዳሉት ምርመራው መስከረም አንድ የሚጀመር ሲሆን በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል።
በሆንግ ኮንግ ምንም እንኳን በአንድ ቀን በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ ቢሆንም በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ሁኔታው አሳሳቢ ነው ብለዋል መሪዋ ።
ይሁን እንጂ ከቻይና በመጡ 60 አባላት ባሉት ቡድን በመታገዝ እየተከናወኑ ባሉ ምርመራዎች ምን ያህል ባለሙያዎች እንደሚሳተፉ
የታወቀ ነገር የለም።
ቤጂንግ ሰኔ ወር ላይ አዲስ ብሔራዊ የፀጥታ ሕግ በሆንግ ሆንግ ላይ ከጣለች በኋላ በሆንግ ሆንግ በሚገኙ የዴሞክራሲ አቀንቃኝ
ቡድኖችና በቻይና መንግሥት መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ነው።
በርካቶችም ይህ ሕግ ነፃነትን ይሸረሽራል ሲሉ ተችተውታል።
ይደረጋል የተባለውን ሰፊ ምርመራ ተከትሎም አንዳንድ የምክር ቤት አባላት ቻይና ምርመራውን ተንተርሳ ለስለላ የዘረ መል ናሙና ልትወስድ ትችላለች የሚል ስጋት አንስተዋል።
መሪዋ ኬሬ ግን አርብ ዕለት "ሀሰተኛ ክስና ስም ማጥፋት ነው" ሲሉ አጣጥለውታል። የተወሰደው ናሙና ከምርመራው በኋላ ይወገዳልም ብለዋል።
በሆንግ ኮንግ ከጥር ወር ጀምሮ ከ4 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን የ75 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
ባለፈው ወር መሪዋ
የሆንግ ኮንግ የምክር ቤት ምርጫ በወረርሽኙ ሳቢያ በአንድ ዓመት ሊራዘም እንደሚችል ተናግረው ነበር።
ሆኖም በቫይረሱ የሚያዙ
ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ በመሆኑ የተራዘመው ጊዜው ረዥም ነው በማለት በርካታ ትችቶች ተሰንዝረዋል።
አርብ ዕለት በአንድ
ቀን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 27 ብቻ ነው።