ዓለም እንዴት ዋለች? አሜሪካ፣ ስፔን ፣ ሰሜን ኮሪያ . . .

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ መረጃ እንደሚያሳው፤ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ16.2 ሚሊዮን አልፏል። ከ648 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸው አልፏል።
ከተለያዩ አገሮች የተውጣጡ ዘገባዎች የሚከተሉት ናቸው፦
·አሜሪካ- በከፍተኛ ደረጃ በወረርሽኙ የተጎዳችው አገር ስትሆን፤ በአጠቃላይ በዓለም በበሽታው ከተያዙ 20 በመቶው አሜሪካ ይገኛሉ።
·ሆንክ ኮንግ- በአንድ ቀን በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ቀድሞ ከተመዘገበው በላይ ሆኗል። በሽታው ማኅበረሰቡ ውስጥ የበለጠ እንዳይሰራጭ፤ ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተግባራዊ እየተደረጉም ነው።
·ቬትናም- ከግንቦት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ አራት ውጪ አገር ዜጎች ላይ ቫይረሱ መገኘቱን ተከትሎ፤ ዳ ኖግ ወደተባለችው ከተማ ጎብኚዎች እንዳይገቡ ተከልክሏል።
·ስፔን- አዲስ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ተለይተዋል። ጎብኚዎች ደህንነት ተሰምቷቸው ወደ ስፔን መሄድ ይችላሉ ተብሏል። በሌላ በኩል ዩኬ የስፔን ተጓዞች ለ14 ቀናት ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ወስናለች።
ሰሜን ኮሪያ- አንድ ሰው በኮሮናቫይረስ ተጠርጥሯል ተብሏል። ግለሰቡ ከሦስት ዓመታት በፊት ወደ ደቡብ ኮሪያ ሸሽቶ የነበረና ድንበር አልፎ የተመለሰ መሆኑን የአገሪቱ ብሔራዊ ጣቢያ ዘግቧል።
















