የኦክስፎርዱ ክትባት ውጤታማ መሆኑ የሚታወቀው በጥቅምት መሆኑ ተገለጸ
በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ እየተሠራ ያለው የኮቪድ-19 ክትባት ውጤታማ መሆኑ የሚታወቀው በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ላይ ነው ተባለ።
አስትራዜንካ የተባለው የመድኃኒት ድርጅት በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ ሁለት ቢሊዮን ክትባት የማምረት እቅድ ይዟል።
በዩናይትድ ኪንግደም፣ በአሜሪካ፣ በብራዚል እና በደቡብ አፍሪካ የተጀመሩ ሙከራዎች ውጤታማ መሆናቸው የሚታወቀውም በቀጣዩ ዓመት ነው።
ድርጅቱ ለቢቢሲ እንዳለው፤ ቢያንስ ለ12 ወራት የሚቆይ በሽታ የመከላከል አቅም እንደሚያዳብር ያምናሉ። ከዚህ በተጨማሪም ለ24 ወራት ወይም ከዚያ በላይ በሽታ መከላከል ያስችላል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ።
ጥናቱ አሁን ባለበት ደረጃ፤ ክትባቱ በሽታ የመከላከል አቅምን እንደሚያለምድ ቢታወቅም፤ ሙሉ በሙሉ ውጤታማ መሆኑ ገና አልተረጋገጠም።
ከአንድ ጠብታ ይልቅ ሁለት ጠብታ የተሻለ ውጤታማ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል።
ሆኖም ግን ክትባቱ ለምን ያህል ጊዜ በሽታ እንደሚከላከል አልታወቀም። በተጨማሪም ለበሽታው በዋነኛነት ተጋላጭ የሆኑ አረጋውያን ላይ ምን ያህል ውጤታማ እንደሚሆን አልታወቀም።

የፎቶው ባለመብት, GETTY IMAGES









