አሜሪካ የኢራን ኻርግ ደሴትን ለመቆጣጠር ያሰበችው ለምንድን ነው?

የፎቶው ባለመብት, Reuters
ትራምፕ ለፋይናንሻል ታይምስ እንደተናገሩት አሜሪካ በኢራን የባሐር ዳርቻ ላይ የምትገኘዋን አነስተኛ ደሴት፣ ኻርግን ልትቆጣጠር ትችላለች።
አሜሪካ በደሴቲቱ ላይ ዓኗን የጣለችው የአገሪቱ ኢኮኖሚ የደም ስር የሆነው ነዳጅ ዋነኛ መተላለፊያ በመሆኑ ነው።
አሜሪካ ደሴቲቱን በቁጥጥሯ ስር ብታውል የኢራንን የነዳጅ ሽያጭ ማስተጓጎል ብቻ ሳይሆን ወደ አገሪቱ ሰፋፊ አካባቢዎች ጥቃት ለመፈጸምም ምቹ ሁኔታ ይፈጥርላታል።
ደሴቲቱን መቆጣጠር የእስላማዊ ሪፐብሊክ አብዮታዊ ዘብ ዋነኛ የገቢ ምንጭ ማቋረጥ ያስችላል፤ ይህም ጦርነት ለማካሄድ እንደሚያስቸግረው የደህንነት ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ማይኪ ኬይ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ደሴቲቱን ለመቆጣጠር የሚደረግ ማንኛውም የአሜሪካ ዘመቻ ትንሽ እንደሚሆን ይጠበቃል ያሉት ደግሞ የስኩል ኦፍ ዋር ፖድካስት አቅራቢ አሮን ማክሌን ናቸው።


