ኢራን የተኩስ አቁም ጥያቄ ማቅረቧን ትራምፕ ተናገሩ

የፎቶው ባለመብት, AFP
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “የኢራን አዲስ አመራር ፕሬዝዳንት” የተኩስ አቁም ጥያቄ አቅርበዋል አሉ።
ፕሬዝዳንቱ ትሩዝ ሶሻል በተባለው ማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ “ይህ ሰው እምብዛም አክራሪ አይደለም። ከእሱ ቀደም ሥልጣን ላይ ከነበሩት በተሻለ አዋቂ ነው” ብለዋል።
ይህንን የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተያየትን በተመለከተ አስካሁን ከኢራን በኩል የተሰጠ አስተያየት የለም።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከዚህ ቀደም ኢራን ለድርር ጥያቄ አቅርባለች ብለው ቢናገሩም ከኢራን በኩል ግን ጥያቄ አለመቅረቡ በግልጽ ሲነገር ነበር።
የኢራን ፕሬዝዳንት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርን ጨምሮ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጦርነቱ በተኩስ አቁም ሳይሆን ሙሉ ለሙሉ በዘላቂነት መቆም እንዳለበት ከስምምነት መደረስ እንዳላበት አሳውቀዋል።
አሁንም ኢራን ከስምምነት የምትደርሰው ድጋሚ ጦርነት እንደማይከፈትባት ዋስትና ሲሰጣት ብቻ መሆኑን ቅድመ ሁኔታ አቅርባለች።
ትራምፕ አክለውም “የሆርሙዝ ወሽመጥ ሲከፈት እና ነጻ ሲሆን የምናስብበት ይሆናል። እስከዚያ ድረስ ግን ኢራንን ወደ ምንምነት ለመለወጥ ማጋየታችንን እንቀጥላለን። ወደ ድንጋይ ዘመን እንመልሳታለን” በማለት ጽፈዋል።
ትራምፕ አዲሱ የኢራን መሪ በማለት በተደጋሚ እያደነቋቸው ያሉት ፖለቲከኛ ማን እንደሆኑ ለማወቅ እዚህ ያንበቡ ከአሜሪካ ጋር ለሚደረገው ንግግር ቁልፍ ሰው እና ቀጣዩ መሪ ይሆናሉ የሚባሉት የኢራን አፈጉባኤ ማን ናቸው?



















