"የአሜሪካ ጥቃት ኢራንን የማንበርከክ እንጂ ከኒውክሌር ጋር ምንም ግንኙነት የለውም"- አያቶላህ ኻሜኒ

አሜሪካ በኢራን የፈጸመችው ጥቃት "ኢራንን እጅ የማሰጠት" እንጂ በጭራሽ ከኒውክሌር ማበልጸግ ጋር ፍጹም ግንኙነት እንደሌለው የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ኻሜኒ ተናገሩ።ከሳምንት በኋላ የታዩት ጠቅላይ መሪው “ሁልጊዜም ቢሆን አንድ ነገር ብቻ ነው ፍላጎታቸው፤ ኢራን እጇን እንድትሰጥ” ብለዋል።

ጭምቅ ሃሳብ

  • እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት የአገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ ሳኢድ ኢዛዲ መገደላቸውን የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ማረጋገጡን የአገሪቱ ሚዲያ ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
  • የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ኢራን ከአሜሪካ ጥቃት በፊት የበለጸገ የዩራኒየም ክምችቷን ከፎርዶ የኒውክሌር ጣቢያ አዛውራለች የሚለውን ሪፖርት አስተባበሉ።
  • በኳታር የአሜሪካ የጦር ሰፈርን ለመከላከል የቀሩት 44 ወታደሮች ብቻ እንደነበሩ አሜሪካ ገለጸች
  • አሜሪካ 'ኦፕሬሽን ሚድናይት ሐመር' በሚል ስያሜ በኢራን ላይ የፈጸመችው ጥቃት ለ15 ዓመታት የታቀደበት እንደሆነ የአገሪቱ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ዳን ኬይን ገለጹ።
  • በኢራን ላይ የተፈጸመው "የተሳካ ታሪካዊ ጥቃት ነበር" ሲሉ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት ገለጹ
  • አሜሪካ በኢራን የፈጸመችው ጥቃት ኢራንን እጅ የማሰጠት እንጂ በጭራሽ ከኒውክሌር ማበልጸግ ጋር ፍጹም ግንኙነት እንደሌለው የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ኻሜኒ ተናገሩ
  • ትራምፕ፤ የአሜሪካ ጥቃት የኢራን ኒውክሌር ይዞታዎችን አላወደመም የሚለውን የደህንነት ግምገማ ውድቅ አደረጉ
  • የአሜሪካ ጥቃት የኢራን ኒውክሌር ይዞታዎችን እንዳላወደመ የደህንነት ግምገማ አሳየ

የቀጥታ ሽፋን

  1. ኢራን አሜሪካ ለፈጸመችው ጥቃት እንዴት ምላሽ ልትሰጥ ትችላለች?

    አሜሪካ ሌሊቱን በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ለፈጸመችው ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ከሦስት ስልታዊ ምርጫዎች አንዱን መምረጥ ይጠበቅባታል። እነዚህ ሦስት ስልታዊ አማራጮች ምንድን ናቸው?

    እጅን አጣጥፎ መቀመጥ- ይህ ከተጨማሪ የአሜሪካ ጥቃቶች ሊጠብቃት ይችላል። እንዲያውም የዲፕሎማሲውን መስመር መምረጥ ከአሜሪካ ጋር እንደገና ድርድር ለመቀመጥ ያስችላታል። ነገር ግን ምንም ነገር አለማድረግ የኢራን አመራርን በተለይም አሜሪካ ጥቃት ከፈጸመች አስከፊ መዘዞች እንደሚደርሱ ካስጠነቀቀ በኋላ ደካማ ያስመስለዋል። አስተዳደሩ በሕዝቡ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት መቀዛቀዝ እና የአሜሪካ ተጨማሪ ጥቃቶች የሚያደርሱትን ኪሳራ በማመዛዘን ሊወስን ይችላል።

    ጠንካራ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት- ኢራን አሁንም ለዓመታት አምርታ የሸሸገቻቸው ከፍተኛ የባለስቲክ ሚሳኤሎች አሏት። ጥቃት ለመሰንዘር የምትወስን ከሆነ በመካከለኛው ምሥራቅ ወደ 20 የሚጠጉ የአሜሪካ ጦር ኃይሎች ይገኛሉ። እንዲሁም በዩናይትድ ስቴትስ የባህር ኃይል መርከቦች ላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ፈጣን ጀልባዎችን ​​በመጠቀም 'ተከታታይ ጥቃት' ልትፈጽም ትችላለች።

    ጊዜ ጠብቆ እና አድብቶ ጥቃት መፈጸም- ·ይህ ማለት አሁን ያለው ውጥረት እስኪበርድ ድረስ መጠበቅ እና የአሜሪካ ጦር ሠፈሮች በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ በማይሆኑበት ጊዜ ድንገተኛ ጥቃት መፈፀም ማለት ነው።

  2. በኢራን ጥቃት 11 ሰዎች መጎዳታቸውን የእስራኤል የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት አስታወቀ

    የእስራኤል የድንገተኛ አደጋ ሠራተኞች

    የፎቶው ባለመብት, MDA

    የእስራኤል የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት ኢራን በፈጸመችው ጥቃት 11 ሰዎች ተጎድተው ወደ ሆስፒታልመወሰዳቸውን ገልጿል።

    ጉዳቱ ከደረሰባቸው ሰዎች መካከል አንድ የ30 ዓመት ሰው በፍንጥርጣሪዎች በላይኛው የሰውነት ክፍሉ ላይ ተመትቶ መካከለኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገልጿል።

    የተቀሩት 10 ሰዎች ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

    የእስራኤል የአየር ኃይል በምዕራብ ኢራንበሚገኙ "ወታደራዊ ዒላማዎች" ላይ አዲስየጥቃት ዘመቻ መጀመሩ ተናግሯል።

    ይህ የሆነው የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ኢራንሚሳዔሎችን ማስወንጨፏን ከገለፀ በኋላ ነው።

    የመከላከያ ኃይሉ አክሎም በኢራን ግዛት በሚሳኤል ማስወንጨፊያዎች ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ብሏል።

  3. ኢራን የአሜሪካን ጥቃቶችን ተከትሎ 'ማቆሚያ የሌለው መዘዝ' ይከተላል ስትል አስጠነቀቀች

    የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰይድ አባስ አራግቺ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰይድ አባስ አራግቺ የአሜሪካን ጥቃት “አስከፊ” ሲሉ አውግዘው፣ኢራን “ሉዓላዊነቷን ለመጠበቅ ሁሉንም አማራጮች እንደምትመለከት” ተናግረዋል።

    በኤክስ ገጻቸው ላይ በለጠፉት ጽሑፍ ላይ "ዛሬ ማለዳ የተከሰተው ጥቃት እጅግ አሳፋሪ እና ማቆሚያ የሌለው መዘዝ የሚያስከትል ነው። እያንዳንዱ እና ሁሉም የተባበሩት መንግሥታት አባል አገራት በዚህ እጅግ አደገኛ፣ሕገወጥ እና የወንጀል ባህሪ ሊደናገጡ ይገባል" ሲል ጽፈዋል።

    አራግቺ አክለውም ዩኤስ የመንግሥታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አባል ሆና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተር ላይ “ከባድ ጥሰት ፈጽማለች” ሲሉ ኮንነዋል።

  4. አሜሪካ ዛሬ ስለፈፀመችው ጥቃት እስካሁን ድረስ ምን እናውቃለን

    ዶናልድ ትራምፕ መግለጫ ሲሰጡ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ወደ ገጻችን ገና አሁኑ መምጣትዎ ከሆነ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ዛሬ ማለዳ ላይ ያሉ አንኳት መረጃዎችን እንዲህ ጠቅለል አድርገን አቅርበንላችኋል።

    • አሜሪካ ኢራን ውስጥ በሚገኙ ሦስት የኒውክሌር ተቋማት፤ ናታንዝ፣ ኢስፋሃን እና ፎርዶ ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ብላለች። ፎርዶ በተራራዎች ውስጥ የሚገኝ እጅግ በጣም ለመድረስ አስቸጋሪ የሆነ ተቋም እንደሆነ ይታመናል።
    • ትራምፕ በቴሌቭዥን ባደረጉት ንግግር ዘመቻውን “አስደናቂ ወታደራዊ ስኬት” ሲሉ አሞካሽተው፣ ቴህራን በፍጥነት ሰላም እንድትፈጥር ወይም “ከዚህ የባሰ” ጥቃት እንደሚደርስባት አስጠንቅቀዋል።
    • አሜሪካ ቢ-2 አውሮፕላኖቿን በመጠቀም ወደ መሬት ሰርስረው የሚገቡ ቦምቦችን በመጠቀም ድብደባ መፈፀሟ የተገለፀ ሲሆን የአገሪቱ መከላከያ በጉዳዩ ላይ ዛሬ መግለጫ ሊሰጥ ይችላል።
    • የኢራን የመንግሥትመገናኛ ብዙኃን ፎርዶ በከፊል "በጠላት ጥቃት ተፈጽሞበታል" ያለ ሲሆን፣የጉዳቱን መጠን ግን አሳንሶ አቅርቧል።
    • ቴህራን ቀደም ሲል አሜሪካ በሁለቱ አገራት ግጭት ውስጥ ጣልቃ የምትገባ ከሆነ በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙየአሜሪካን ጦር ሠፈሮች ላይ ጥቃት እንደምታደርስ አስጠንቅቃለች።
    • እስራኤልየአሜሪካን ጥቃት መደሰቷን የገለፀች ሲሆን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ "ድፍረት የተሞላበት ውሳኔ" እና "የታሪክንሂደት የሚለውጥ" ሲሉ አንቆለጳጵሰውታል።
    • በአሜሪካ ሪፐብሊካኖች የትራምፕን እርምጃ ሲያወድሱ ዲሞክራቶች ደግሞ አሜሪካ ወደ ሌላ "ማብቅያ ወደሌለው" ጦርነት እየገባች ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
    • ኢራን አሜሪካ ለፈፀመችው ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ሚሳዔሎችን መተኮሷ ተሰምቷል።

    በእስራኤል እና ኢራን ግጭት አዳዲስ መረጃዎችን እና ትንታኔዎችን እንዲሁም ፎቶዎችን እናቀርብላችኋለን አብራችሁ ቆዩ

  5. ዲሞክራቶች የትራምፕን እርምጃ 'ያለ ኮንግረስ ፍቃድ' የተደረገ ጣልቃ ገብነት ሲሉ አወገዙ

    የኮንግረስ አባሏ አሌክሳንድሪያ ኦካሲዮ ኮርትዝ

    የፎቶው ባለመብት, EPA

    አንዳንድ ዲሞክራት ሕግ አውጭዎች አሜሪካ የኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ የፈፀመችውን ድብደባ ያለ ኮንግረስ ይሁንታ የተፈፀሙ ናቸው ሲሉ አወገዙ።

    የኮንግረስ አባሏ አሌክሳንድሪያ ኦካሲዮ ኮርትዝ ይህ ሕገ መንግሥቱን እና የኮንግረሱን ሥልጣን "በከባድ ሁኔታ መጣስ" እና "ፍፁም እናግ ልጽ በሆነ መልኩ ክስ ለመመስረት የሚያስችል ነው" ብለዋል።

    በኤክስ ገጻቸው ላይ “ለትውልድ ሊከተለን የሚችል ጦርነት ለመክፈት በግዴለሽነት አደጋ ላይ ጥለውናል” ብለዋል።

    የአሜሪካ የኮንግረስ አባሏ ራሺዳ ተላይብም የአሜሪካን ሕገ መንግሥትን “በግልፅ መጣስ” ያሉትን ድርጊት አውግዘው ኮንግረስ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቀዋል።

    "በመካከለኛው ምሥራቅ ለአስርት ዓመታት የተካሄደው ማለቂያ የሌለው ጦርነት የት እንዳደረሰን አይተናል፤ሁሉም በ"ጅምላ ጨራሽ መሳሪያ" ውሸት ላይ የተመሰረተ ነበር። ዳግም በዚያ መንገድ አንታለልም” ብለዋል።

    ሌላኛው የኮንግረስ አባል ጂም ማክጎቨርን በበኩሉ ሁኔታውን “እብደት” ብለውታል።

    "ትራምፕ ኢራንን ያለ ኮንግረስ ይኹንታ ደብድበዋል፣ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ጎትቶናል። አሁንም መማር ያለብንን አልተማርንም?"

  6. ሐማስ የአሜሪካን 'ግልጽ ጥቃት' አወገዘ

    ሐማስ አሜሪካ በኢራን ላይ የፈጸመችውን የአየር ድብደባ “ግልጽ ጥቃት” ሲል ገልጾታል።

    ሐማስ በመግለጫው ላይ ጥቃቱ "በጉልህ የዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ እና ለዓለም አቀፍ ሰላም እና መረጋጋት ቀጥተኛ አደጋ ነው" ብሏል።

    ሐማስ መስከረም 26/2016 ዓ.ም. በእስራኤል ላይ ጥቃት በማድረስ 1,200 ያህል ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል።

    እስራኤል በምላሹ በጋዛ እያካሄደች በምትገኘው ወታደራዊ ጥቃት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

    ሐማስ፣ የፍልስጤም የታጠቀ ቡድን እና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሲሆን በአሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና እስራኤልን ጨምሮ በብዙ አገራት በአሸባሪነት ተፈርጇል።

  7. የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ የአሜሪካን ጥቃት “አደገኛ ማባባስ” ነው አሉ

    የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አሜሪካ በኢራን የኒውለክሌር ተቋማት ላይ ለፈጸመችው ጥቃት ምላሽ ሰጠ።

    የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ የፈጸመችውን ጥቃት “አደገኛ ማባባስ” ሲሉ የገለፁት ሲሆን በአሁኑ ጊዜ “ይህ ግጭት በፍጥነት ከቁጥጥር ውጭ ሊወጣ የሚችልበት ስጋት እየጨመረ ነው፤በሰላማዊ ዜጎች፣ በአካባቢው እና በዓለም ላይ አስከፊ መዘዝ አለው” ብለዋል።

    ዋና ፀኃፊው በኤክስ ልጥፋቸው ላይ "በዚህ አደገኛ ሰዓት ውስጥ የቀውስ ሽክርክሪትን ማስወገድ በጣም አስፈላጊ ነው። ምንም ዓይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለም። ብቸኛው አማራች ዲፕሎማሲ ነው። ብቸኛው ተስፋ ሰላም ነው" ሲሉ አስፍረዋል።

  8. የእስራኤል ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የትራምፕ ስም በታሪክ መዝገብ ላይ በወርቅ ይጻፋል አሉ

    የእስራኤል ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳኣር አሜሪካ በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ የትራምፕ ስም በታሪክ መዝገብ ላይ በወርቅ ይጻፋል አሉ።

    በኤክስ ገጻቸው ላይ በለጠፉት በዚህ አስተያየታቸው ፕሬዚደንቱ ጥቃቱን ለመፈጸም “ድፍረት የተሞላበት ውሳኔ” በመውሰዳቸው አሞካሽተውታል።

    አክለውም የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒሰትር ኔታንያሁ ይህንን “ታሪካዊ ውሳኔ” መርተውታል ብለዋል።

  9. የአሜሪካው ፕሬዚደንት እና ባለሥልጣኖቻቸው በኢራን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በቀጥታ ሲከታተሉ

    የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና ሌሎች ባለሥልጣናት በኢራን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በቀጥታ ሲከታተሉ የሚያሳዩ ምስሎች ወጥተዋል።

    በጥቃቱ ሦስት የኢራን የኒውክሌር ተቋማት በቦምብ መደብደባቸው የተገለፀ ሲሆን ከእነዚህ መካከልም ፎርዶ ይገኝበታል።

    እስካሁን ድረስ በፎርዶ ላይ ስለደረሰው የጉዳት መጠን ኢራን ያለችው ነገር የለም።

    ዶናልድ ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የአሜሪካ የጦር ጄኔራል

    የፎቶው ባለመብት, THE WHITE HOUSE

    የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ

    የፎቶው ባለመብት, THE WHITE HOUSE

    የአሜሪካ የጦር ጄነራል

    የፎቶው ባለመብት, THE WHITE HOUSE

    የአሜሪካው ፕሬዚደንት እና ምክትላቸው ቫንስ

    የፎቶው ባለመብት, THE WHITE HOUSE

  10. አሜሪካ በኢራን የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት ፈጸመች

    የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ መከላከያ ኃይል በኢራን ሦስት የኒውክሌር ተቋማት ላይ የቦምብ ድብደባ መፈፀሙን ተናገሩ።

    ፕሬዚደንቱ ለመካከለኛው ምሥራቅ ግጭት የሁለት ሳምንት ጊዜ ሰጥተው የነበረ ቢሆንም፣ ይህንን በተናገሩ በሁለተኛው ቀን ጥቃት ፈጽመዋል።

    ይህ የአሜሪካ ጥቃት በኢራን እና በእስራኤል መካከል ያለውን ግጭት እንዳያባብሰው ተሰግቷል።

    ዶናልድ ትራምፕ ከጥቃቱ በኋላ በዋይት ሐውስ በሰጡት አጭር መግለጫ “አስታውሱ፣ በርካታ ዒላማዎች ገና ይቀሩናል። በሁሉም መመዘኛ የዛሬው ምሽቱ ከባዱ እና ደግሞ በጣም አደገኛው ነበር” ብለዋል።

    ፕሬዚደንቱ በዚሁ ንግግራቸው “ሠላም በፍጥነት የማይመጣ ከሆነ ወደ ሌሎቹ ዒላማዎችቻው በፍጥነት እና በክህሎት እንሄዳለን” ሲሉ ዝተዋል።

    ዛሬ አሜሪካ ጥቃት ከፈጸመችባቸው የኒውክሌር ተቋማት መካከል አንዱ በተራራዎች መካከል የተደበቀው ፎርዶ ይገኝበታል።

    በተቋሙ ላይ ስለደረሰው ጉዳት እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

  11. የእስራኤል እና የኢራን ግጭትን በተመለከተ የወጡ የቅርብ መረጃዎች

    የአደጋ ሠራተኞች በእስራኤል ጥቃት በደረሰበት ሥፍራ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, የእስራኤል ባለሥልጣናት ኢራን ቤት ሺያን ላይ ላደረሰችው ጥቃት ምላሽ ሰጥተዋል

    የእስራኤል እና የኢራን ግጭትን በተመለከተ ዛሬ አዳዲስ መረጃዎች እየወጡ ነው። የተወሰኑትን እናጋራችሁ፡-

    በኢራን

    • የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ የአሜሪካ በግጭቱ መሳተፍ "እጅግ አደገኛ ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
    • ለዲፕሎማሲያዊ ንግግር ከኢራኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አጋርቺ ጋር በኢስታንቡል የተገናኙት የቱርኩ ፕሬዚደንት ሪሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን፣ "እስራኤል ለመካከለኛው ምሥራቅ ሰላም ትልቋ እንቅፋት ናት" ብለዋል።
    • የኢራን ጤና ሚኒስቴር ከስምንት ቀናት በፊት ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ ቢያንስ 430 ሰዎች መገደላቸውን ገልጿል።

    በእስራኤል

    • የእስራኤል ጦር ዒላማ አድርጎ በፈፀመው ጥቃት ሁለት የኢራን የጦር አዛዦችን መግደሉን አስታውቋል።እነዚህም የሃማስ አስተባባሪ ሳኢድ ኢዛድ እና የኩዱስ ኃይል አዛዥ የሆኑት ቤህናም ሻህሪያሪ ናቸው ብሏል።
    • የእስራኤል መከላከያ ኃይል ስምንት የኢራን ድሮኖች ዛሬ ጠዋት ላይ ወደ እስራኤል የአየር ክልል መብረራቸውን ገልጿል።
    • እስራኤል ግጭቱ ከጀመረ አንስቶ በልብ ህመም የሞተን ጨምሮ 25 ሰዎች መገደላቸውን እና 2ሺህ 517 ሰዎች መቁሰላቸውን አስታውቃለች።

    በሌላ በኩል ደግሞ የአሜሪካ የብሔራዊ ደኅንነት ዳይሬክተር ቱልሲ ጋባርድ አሁን ላይ ኢራን “በሳምንታት ውስጥ” ኒውክሌር ልትሰራ ትችላለች ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

    ፕሬዚደንት ትራምፕ ግን ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እየገነባች ስለመሆኗ ምንም ዓይነት መረጃ ባለመኖሩ የብሔራዊ ደኅንነት ዳይሬክሯ “ ተሳስተዋል” ሲሉ ትናንት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

  12. "እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ናት"- የቱርክ ፕሬዚዳንት

    ፕሬዚዳንት ረሲብ ጣይብ ኤርዶጋን

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ኢራንና አሜሪካ ሊያደርጉት ከነበረው አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ሊጀመር ሲል እስራኤል በኢራን ጥቃት መፈጸሟ ሆን ብላ “ውይይቱን ለማበላሸት” እንደሆነ የቱርኩ ፕሬዚዳንት ረሲብ ጣይብ ኤርዶጋን ተናገሩ።

    የቱርኩ ፕሬዚዳንት ይሄንን ያሉት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።

    ኤርዶጋን የእስራኤልን “የሽፍተኝነት ተግባር” አውግዘው ፤ መካከለኛውን ምስራቅ ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ወቅሰዋል።

    የኔታንያሁ መንግሥት “ለአካባቢው ሰላም ትልቁ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጠ ነው” ነው ሲሉ ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ተችተዋል።

    አክለውም “የኔታንያሁ መንግሥት ሰኔ 6 ላይ የፈጸመው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው” ብለዋል።

  13. ኢራን፣ በእስራኤል ጥቃት እስካሁን ቢያንስ 430 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀች

    በኢራን ላይ የተፈጸመው ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ኢራን ግጭቱ ከተጀመረበት፣ ከሰኔ 6/ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በእስራኤል ጥቃት ቢያንስ 430 ሰዎች መገደላቸውን አስታወቀች።

    ከሟቾች በተጨማሪም 3 ሺህ 500 ሰዎች መቁሰላቸውን የኢራን ጤና ሚኒስትርን ዋቢ አድርጎ ኑር የዜና ወኪል ሪፖርት አድርጓል።

    በግጭቱ የተገደሉ ሰዎችን በተመለከተ ሚኒስትሩ ከቀናት በኋላ ያወጣው ይፋዊ አኃዝ ነው።

    ሚኒስቴሩ ባለፈው ሳምንት እሁድ ቢያንስ 224 ሰዎች መገደላቸውን ገልጾ ነበር።

    የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በበኩላቸው በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎችን ቁጥር 657 አድርሶታል።

    በእስራኤል ደግሞ ግጭቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ኢራን ባስወነጨፈቻቸው ሚሳኤሎች አንዲት በልብ ድካም የሞተችን ጨምሮ 25 ሰዎች መገደላቸው ተገልጿል።

    እንዲሁም 2 ሺህ 517 ሰዎች መቁሰላቸውን እስራኤል አስታውቃለች።

  14. በእስራኤል ጥቃት የተመቱት የአያቶላህ ኻሜኒ አማካሪ መትረፋቸው ተነገረ

    የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አማካሪ አሊ ሻምካኒ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እስራኤል በቴህራን ጥቃት በጀመረችበት፣ ከዘጠኝ ቀናት በፊት ተመትተው የነበሩት እና ተገድለዋል ተብሎ ታስቦ የነበረው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አማካሪ አሊ ሻምካኒ መትረፋቸውን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግበዋል።

    የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ አሊ ሻምካኒ በእስራአል ጥቃት የደረሰባቸው ሰኔ 6/ 2017 ዓ.ም ነበር። አማካሪው በአሁኑ ወቅት በሆስፒታል ውስጥ በማገገም ላይ እንደሆኑ እና በተረጋጋ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ መንግሥታዊ የኢራን የዜና ወኪል ዘግቧል።

    በሻምካኒም ኤክስ ገጻቸው ላይ ዛሬ ጥዋት በተለጠፈ ጽሁፍ ከጥቃቱ ተርፌያለሁ ብለዋል።

    “ቆስዬ መትረፍ እጣ ፈንታዬ ነበር፤ እናም ተርፌያለሁ። ጠላቶቻችንም ጥላቻቸው ይቀጥላል። ለኢራን መቶ ጊዜ ራሴን እሰዋለሁ” ይላል።

  15. እስራኤል አዲስ በፈጸመችው ጥቃት የኢራን ጦር ከፍተኛ አዛዥ መግደሏን አስታወቀች

    እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ አገራቸው በኢራኗ ቆም ከተማ በአፓርታማ ላይ በፈጸመችው ጥቃት የኢራን ከፍተኛ የጦር አዛዥ መገደላቸውን ተናገሩ።

    ሚኒስትሩ አዛዡ ሳኢድ ኢዛዲ ሐማስን በማስታጠቅ እና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነት ነበራቸው ሲሉ ቅዳሜ ዕለት መናገራቸውን የአገር ውስጥ ሚዲያዎች አና ሮይተርስ ዘግቧል።

    “ይህ ለእስራኤል የስለላ እና የአየር ኃይል ትልቅ ስኬት ነው። ፍትህ ለተገደሉት እና ለታጋቾች። የእስራኤል ረጅም ክንድ ጠላቶቿን ሁሉ ይደርሳል” ብለዋል።

    ሳኢድ ኢዛዲ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ቅርንጫፍ የሆነው ኃያሉ 'ቁድስ ፎርስ' አባል ነበሩ። ይህ ቅርንጫፍ በቀጣናው ያሉ የኢራን አጋር ታጣቂዎችን ድጋፍ ማድረግን ጨምሮ በውጭ አገራት ያሉ እንቅስቃሴዎችን በበላይነት የሚያይ ነው።

  16. ትራምፕ የአገራቸው የብሔራዊ መረጃ በኢራን ኒውክሌር መርሃ ግብር ላይ ያለው መረጃ የተሳሳተ ነው አሉ

    ፕሬዚዳንት ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የአሜሪካ ብሔራዊ መረጃ ዳይሬክተር ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እየገነባች እንደሆነ የሚጠቁም ምንም መረጃ የለም ማለታቸውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ፕሬዚዳንት ትራምፕ “የተሳሳተ መረጃ ነው” የሚል ምላሽ ሰጡ።

    የብሔራዊ መረጃ ዳይሬክተር የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብርን ገምግመው የጦር መሳሪያ የሚጠቁም ምንም መረጃ እንደሌለ መናገራቸውን ተከትሎ እርስዎ ምን መረጃ አለዎት? የሚል ጥያቄ ትራምፕ ተጠይቀዋል።

    "ይህ ከሆነ የስለላ ማህበረሰቡ ተሳሳቷል፤ ከመረጃ ማህበረሰቡ ውስጥ ማን ነው እንዲህ ያለው” ሲሉ ትራምፕ በምላሹ ጥያቄ አቅርበዋል

    የጠየቃቸው ሪፖርተር ይህንን ያሉት የብሔራዊ መረጃ ዳይሬክተሯ ቱልሲ ጋባርድ መሆናቸውን በነገራቸው ወቅት

    “ተሳስታለች” የሚል ፈጣን ምላሸ ሰጥተዋል።

    ጋባርድ የአሜሪካ የመረጃ ኤጀንሲዎች ኢራን በአውሮፓውያኑ 2003 ዕግድ የተጣለባትን የኒውክሌር የጦር መሳሪያ መርሃ ግብር አለመቀጠሏን ማረጋገጣቸውን በመጋቢት ወር ለኮንግረሱ አስረድተው ነበር።

    ኢራን የኒውክሌር ማበልጸግ ስራዋን ለሲቪል አላማዎች እንደምትጠቀምበት ስታስታውቅ ቆይታለች።

  17. የእስራኤል ጦር ኢራንን ለማጥቃት ለዓመታት አቅዶ መዘጋጀቱን አስታወቀ

    የእስራኤል ጦር ኃይል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ኢያል ዛሚር

    የፎቶው ባለመብት, IDF

    የእስራኤል መከላከያ ኃይል በኢራን ላይ ጥቃት ለመፈጸም ለአመታት ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ።

    የእስራኤል ጦር ኃይል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ኢያል ዛሚር ከቅርብ ወራት ወዲህ ይህ የጥቃት ዝግጅት “ከበድ ባለ ሚስጥራዊ ሁኔታ” እንዲፋጠን ተደርጓል ብለዋል።

    ዝርዝር መረጃ ያልሰጡት ኤታማዦር ሹሙ ወታደራዊ ዘመቻው ሊሳካ የቻለው “ተግባራዊ እና ስትራቴጂካዊ ሁኔታዎች በመጣጣማቸው ነው” ብለዋል።

    አክለውም ይህ ጥቃት ቢዘገይ ኖሮ “እነዚህ ሁኔታዎች ሊታጡ እንደሚችሉ” እና እስራኤልን አደጋ ላይ የሚጥል ነው ብለዋል።

    “ለከባድ እና ድንገተኛ ጥቃት ምስጋና ይግባውና ድንቅ ውጤቶችን አስመዝግበናል” ብለዋል።

  18. ኢራን ዲፕሎማሲውን የምታጤነው የእስራኤል ጥቃት ሲቆም እንደሆነ አስታወቀች

    የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አርጋቺ

    የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አርጋቺ አገራቸው “የእስራኤል ጥቃት ሲቆም ብቻ ነው ወደ ዲፕሎማሲው የምትመለሰው” ሲሉ ከፈረንሳይ፣ ዪናይትድ ኪንግደም፣ ጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ውይይት ተናገሩ።

    ሚኒስትሩ “ጥቃት ፈጻሚው ላደረሳቸው አሰቃቂ ወንጀሎች ተጠያቂ ሊሆን ይገባል” ሲሉም አቋማቸውን አስረድተዋል።

    ሚኒስትሩ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ሰላማዊ እንደሆነ እና በጣቢያዎቹ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች አለም አቀፍ ህግን የጣሰ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

    ኢራን “ራሷን የመከላከል ህጋዊ መብቷን መጠቀሟን ትቀጥላለች” ያሉት ሚኒስትሩ አክ “የኢራን የመከላከል አቅም ለድርድር የማይቀርብ መሆኑን ግልጽ አደርጋለሁ ሲሉ አስረድተዋል።

    የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከእስራኤል ጋር ያለውን ግጭት ለማስቆም ፈረንሳይን ጨምሮ አውሮፓውያኑ አገራት ለኢራን የዲፕሎማሲ ፕሮፖዛል እንደሚያቀርቡ ተናግረው ነበር።

    በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል የተባለው ፕሮፖዛል፦

    • የዓለም አቀፉየአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) በኢራን ስራውን እንዲጀምር እና የዩራኒየምን ማበልጸግ ስራ ወደ ዜሮ ማሸጋገር
    • የኢራንን የባለስቲክ ሚሳኤልእንቅስቃሴ መቆጣጠር
    • ኢራን በቀጣናው ላሉተዋጊ ቡድኖች የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ በተመለከተ
    • በኢራን ውስጥ ያሉ “ታጋቾችን” ነጻ ማውጣት ይህም በኢራን እስር ቤቶች ውስጥ የታሰሩ የውጭ ዜጎችን የሚመለከት ነው
  19. ፕሬዚዳንት ፑቲን ለእስራኤል እና ኢራን ግጭት መፍትሄ ማግኘት ይቻላል አሉ

    የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለእስራኤል እና ኢራን ግጭት መፍትሄ ማግኘት እንደሚቻል እና ሩሲያ ሁለቱንም አገራት በማናገር ላይ መሆኗን አሳወቁ።

    ፕሬዚዳንት ፑቲን በሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር “የራሳችን ፕሮፖዛል አለን” ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ሞኒተሪንግ ዘግቧል።

    ሆኖም “በምንም መንገድ ቢሆን እያደራደርን እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል። አሁን እያደረግን ያለነው ሃሳቦችን ማቅረብ ነው” ብለዋል።

    ፑቲን አክለውም “ለሁለቱም አገራት ተቀባይነት ያላቸው መፍትሄዎችን ማግኘት ይቻላል። በኔ አስተያየት እንዲህ አይነት መፍትሄ አለ” ሲሉም አስረድተዋል።