ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ትምህርት ቤት ላይ ስለተፈጸመው ጥቃት ገና ምርመራ እየተደረገ ነው አሉ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ውስጥ በሚናብ የወታደራዊ ካምፕ አቅራቢያ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ ስለተፈጸመው ጥቃት ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ተናገሩ።
ትራምፕ በጥቃቱ ስለሞቱት 168 ሰዎች ኃላፊነት ይወስዱ እንደሆን ተጠይቀው ነበር። ከሞቱት መካከል 110 የሚሆኑት ሕጻናት ናቸው።
ፕሬዝዳንቱ በዚህ ጥቃት ጥቅም ላይ የዋለው ቶማሃውክስ የተባለው ሚሳኤል መሆኑን ገልጸዋል። ሚሳኤሉ በአሜሪካ የተሠራ ሲሆን ኢራንን ጨምሮ ሌሎች አገራትም ይጠቀሙበታል ብለዋል።
በትምህርት ቤቱ ላይ ጥቃት የፈጸመው ሚሳኤል በአሜሪካ ተመርቶ ሌሎች አገራትም ታጥቀውታል የሚለውን ሃሳብ በመስጠት ትራምፕ ብቸኛው ባለሥልጣን ናቸው።
ባለሙያዎች ደግሞ እስራኤልም ሆነች ኢራን ቶማውክስ ሚሳኤል አለመታጠቃቸውን ገልጸዋል።
“ስለጉዳዩ በበቂ አላውቅም” ያሉት ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ ጉዳዩ በመጣራት ላይ ነው ብለዋል።
“የሚመጣው ሪፖርት ምንም ይሁን ምን ሪፖርቱን ለመቀበል ዝግጁ ነኝ” በማለት አክለዋል ፕሬዝዳንት ትራምፕ።






















