
የፎቶው ባለመብት, Reuters
ባለፉት ሳምንታት በእስራኤል
ያልተቋረጠ ጥቃት ምክንያት ከባድ ውድመት በደረሰባት በጋዛ
ሰሜናዊ ክፍል ውስጥ ያሉ ከፊል አካባቢዎች በአሁኑ ጊዜ ለመኖሪያነት እንደማይሆኑ የመንግሥታቱ ድርጅት ገለጸ።
በጋዛ የድርጅቱ የስደተኞች
ጉዳይ ዳይሬክተር የሆኑት ቶማስ ዋይት ይህንን ያሉት በሰሜናዊ የጋዛ ክፍል እና በጋዛ ከተማ ዙሪያ ያሉ አካባቢዎችን ከጉብኙ በኋላ
ነው።
እስራኤል የእግረኛ
ሠራዊት ዘመቻ በጋዛ ላይ በጀመረችበት ጊዜ በሰሜናዊ ጋዛ የሚገኙ ሲቪሎች ከአካባቢው ለቀው እንዲወጡ ካዘዘች በኋላ በምድር እና
በአየር ከባድ ጥቃቶችን ስትፈጽም መቆየቷ ይታወቃል።
ዳይሬክተሩ ለቢቢሲ
ራዲዮ 4 እንደተናገሩት “በደህናው ጊዜ ሞቅ ያለ የሕዝብ እንቅስቃሴ የሚካሄድባት ከተማ፣ ዛሬ መንገዶቿ በፍርስራሾች ተሸፍነዋል”
ብለዋል።
ጨምረውም በከተማዋ
ዳርቻዎች በሚገኙ አካባቢዎች ያሉ ሁሉም ሕንጻዎች ፈራርሰው በመንገዶች ላይም የሚንቀሳቀስ ሰው እንደማይታይ ተናግረዋል።
ቶማስ ዋይት በጋዛ
ውስጥ በተመለከቷቸው እና ውስን ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች “ጥቂት ሰዎች ከሱቆች በር ላይ እና ከቤታቸው ደጅ ተቀምጠው” በማየታቸው
የሕይወት ምልክቶች ቢመለከቱም ከተማዋ “ጸጥ ረጭ” እንዳለች ገልጸዋል።
የመንግሥታቱ ድርጅት
ቡድን በሰሜናዊ ጋዛ ወደሚገኘው ጃባሊያ የእርዳታ አቅርቦት ለማድረስ የተጓዘ ሲሆን፣ “በመጨረሻም አንዳች አይነት ድጋፍ በማግኘታቸው
ነዋሪዎች ታላቅ እፎይታ ተሰምቷቸዋል” ብለዋል ዳይሬክተሩ።
በሰሜናዊ ጋዛ ባደረጉት
ጉብኝትም “ከፍተኛ መጠን ያለው ውድመት የደረሰባቸው” የተወሰኑ አካባቢዎች ለሰዎች መኖሪያ መሆን ከማይችሉበት ደረጃ ላይ እንደደረሱ
አመልክተዋል።
በአንጻራዊነት ደግሞ
በጥቃቶቹ “ያልተነኩ የሚመስሉ” ሌሎች አካባቢዎች ቢኖሩም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል እና ውስን የውሃ አቅርቦት ብቻ ስላላቸው ችግር ውስጥ
መሆናቸውን ተናግረዋል።
በተጨማሪም “ሁሉም
መደበኛ አገልግሎቶች እና እንቅስቃሴዎች…ጋዛ ውስጥ የሉም” ብለዋል የመንግሥታቱ ድርጅት ባለሥልጣን።