ግብፃውያን ወረርሽኙ ሳይገታቸው ድምጽ እየሰጡ ነው

የፎቶው ባለመብት, EPA
ግብፃውያን ራሳቸውን ከኮቪድ-19 የሚከላከሉባቸው መንገዶች ተመቻችተው ለአዲስ ብሔራዊ ምክር ቤት ድምጽ እየሰጡ ይገኛሉ።
ለመራጮች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እንዲሁም ጓንት መዘራጀቱ ተዘግቧል። በተጨማሪም የራሳቸውን እስኪርብቶ እንዲያዘጋጁና ከሌሎች መራጮች ራቅ ብለው እንዲቆሙም ተደርጓል።
ግብፅ ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ በኮቪድ-19 በተያዙ ሰዎች ቁጥር ከአፍሪካ ሁለተኛዋ ናት።
ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ አገሮች በወረርሽኙ ሳቢያ ምርጫ እንዲራዘም ቢወሰንም፤ እንደ ሲሪ ላንካ እና ቤላሩስ ያሉ አገሮች ምርጫ ለማካሄድ ወስነዋል።
‘ኢንስቲትዮት ፎር ዴሞክራሲ አሲስታንስ’ የተባለ ድርጅት እንዳለው፤ 69 አገሮች እና ግዛቶች በኮሮናቫይረስ ሳቢያ ምርጫ ሲያራዝሙ ከ50 በላይ ደግሞ ምርጫ እንዲከናወን ውሳኔ አሳልፈዋል።
የግብፅ የምርጫ ውጤት ነሐሴ 19 ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።














