በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 21 ሺህ ተጠጋ

በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የማህበረሰብ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ተከትሎ በአገሪቱ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 21 ሺህ ተጠግቷል። ይህንንም ተከትሎ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በተሻለ ሁኔታ ለመቆጣጠር "ማኅበረሰብ አቀፍ ንቅናቄና ምርመራ ዘመቻ" በትናንትናው ዕለት የብሄራዊ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ በይፋ አስጀምረዋል።ዘመቻው አገር አቀፍ ንቅናቄ በማድረግ ማህበረሰቡ የመከላከያ መንገዶችን በሃላፊነትና በንቃት እንዲተገብር የሚያስችል እና ሰፊ ምርመራ በማድረግ የወረርሽኙን ሁኔታ ይበልጥ በማወቅ ቀጣይ ሁኔታዎችን ለመወሰን የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል። "ማንም" የሚል ስያሜ የተስጠው ዘመቻ ለአንድ ወር የሚቆይ ሲሆን በነሃሴ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት 200 ሺህ ሰዎችን የመመርመር ዕቅድ ተይዟል። አገሪቷ እስካሁን ድረስ 444 ሺህ 226 የላብራቶሪ ምርመራዎችን አከናውናለች።

የቀጥታ ሽፋን

  1. ተጨማሪ 459 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው በምርመራ ተረጋገጠ

    ግራፊክስ

    በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 459 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴርና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።

    በመግለጫው ላይ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ7319 ናሙናዎች ምርመራ መደረጉ ተጠቅሶ ከእነዚህ መካከልም 459 ሰዎች በቫይረሱ መያዛው መረጋገጡ ተገልጿል።

    ከዚህም በተጨማሪ 13 ሰዎች ህይወታው ሲያልፍ 358 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ማገገማቸው ይፋ ሆኗል።

    በተጨማሪም በኮሮናቫይረስ ከተያዙ ግለሰቦች መካከል 185 ሰዎች በጽኑ ሕሙማን ክፍል ውስጥ የሕክምና ክትትል እያገኙ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።

    በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 356 የደረሰ ሲሆን እስካሁን በኮቪድ-19 የተያዙት ደግሞ 20 ሺህ 336 እንደደረሰ የጤና ሚኒስቴር እለታዊ መግለጫ ያሳያል።

    የኮሮናቫይረስ በኢትዮጵያ መገኘቱ ከተረጋገጠ አንስቶ እስካሁን ድረስ ለ459 ሺህ 746 ናሙናዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ተደርጎላቸዋል።

  2. የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት የአካል ብቃት እንቅስቃሴን የሚያሳይ ቪዲዮ ለቀቁ

    የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ፣ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ሰዎች በቤታቸው በመሆን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በመስራት፣ ጤንነታቸውን እንዲጠብቁ ግንዛቤ ለመፍጠር የሚረዳ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ ለቀቁ።

    የ75 ዓመቱ ፕሬዝዳንት በባዶ እግራቸው በመሆን በሰፊው ቤታቸው ውስጥ ዱብ ዱብ ካሉ በኋላ ሌላ ሰው እየቆጠረላቸው 40 ፑሽ አፕ ሲሰሩ ይታያል።

    ፕሬዝዳንቱ በመልክታቸው ይህ ለወጣቶች የቀረበ ፈተና ነው ብለዋል። አንዳንድ ሰዎች ግን ይህ የፕሬዝዳንቱ ተግባር አልጣማቸውም።

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    ፕሬዝዳንቱ በሚያዚያ ወር የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ ከቤት ውጪ የሚደረግ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ከከለከሉ በኋላ ተመሳሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ለቅቀው ነበር። ይህ የእንቅስቃሴ ገደብ በሰኔ ወር ላይ ተነስቷል።

    ኡጋንዳ በታህሳስ ወር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ ያቀደች ሲሆን፣ የአገሪቱ ምርጫ ኮሚሽን ተፎካካሪ ድርጅቶችና ግለሰቦች መራጮቻቸውን በቴሌቪዥን እና በሬዲዮ ብቻ እንዲቀሰቅሱ በማዘዝ በአካል የሚደረግ የምረጡኝ ዘመቻን አግዷል።

  3. የመጠጥ ሽያጭ የከለከለችው ኬንያ እንግዶች በሆቴል ክፍላቸው እንዲጠጡ ፈቀደች

    ተስከር መጠጥ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የኮሮናቫይረስ የማህበረሰብ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ ጭማሬ ማሳየቱን ተከትሎ ይህንን ለመግታት ኬንያ መጠጥ ቤቶቿን ዘግታለች፣ በሬስቶራንቶችና በሆቴሎችም እንዲሁም በመዝናኛ ቦታዎች መጠጥ እንዳይሸጥ የሚል ውሳኔም አስተላልፋለች።

    ነገር ግን የኬንያ ቱሪዝም ሚኒስትር እንዳሳወቁት እንግዶች በሆቴላቸው ክፍል ውስጥ ሆነው መጠጥ መጠጣት ይችላሉ ብለዋል። ሚኒስትሩ ነጂብ ባላላ እንደገለፁት ሆቴሎች በክፍላቸው ውስጥ ላሉ እንግዶች መጠጥ መሸጥ እንደሚችሉም አስምረዋል።

    ሚኒስትሩ አክለውም ከክፍላቸው ውጭ ላሉ እንግዶች ሆቴሎች መጠጥ እንዳያቀርቡም አስጠንቅቀዋል።

    ሬስቶራንቶችም ሆነ ሌሎች መዝናኛ ቦታዎች መመሪያዎቹን ሊከተሉ ይገባልም ብለዋል።

    ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሰዓት እላፊ አዋጁን ባራዘሙበት ወቅት ነው የመጠጥ ሽያጭ እግዱን ያሳወቁት።

  4. “የኑሮ ውድነቱ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልገዋል”

  5. በዓለም ዙሪያ በኮሮናቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ700ሺህ ተሻገረ

    የሞቱ ሰዎች

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እንደ ጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ አሃዝ ከሆነ በመላው ዓለም ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ700ሺህ ተሻግሯል።

    ከአጠቃላዩ አሃዝ 156ሺህ ገደማ የሚሆኑት የተመዘገበው በአሜሪካ ነው። ብራዚል ከ95 በላይ ዜጎቿን ስታጣ ሜከሲኮ ከ48ሺህ በላይ፣ ዩናይትድ ኪንግደም 46ሺህ እንዲሁም ሕንድ ወደ 40ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን በቫይረሱ ሳቢያ በሞት ተነጥቀዋል።

    በቫይረሱ የሚያዙ እንዲሁም በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው የሚልፍ ሰዎችን ትክክለኛ አሃዝ ግን ማወቅ አስቸጋሪ እንደሆነ ባለሙያዎች ያሳስባሉ።

    ለምሳሌ በብራዚል ብዙ የኮሮናቫይረስ ምርመራ እየተከናወነ ስላልሆነ፤ በብራዚል ሪፖርት ከተደረገው አሃዝ በላይ ቦቪድ-19 የተያዙ እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ።

  6. ኢትዮጵያ ቬንቲሌተሮች ከአሜሪካ ተለገሰላት

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የአሜሪካ መንግሥት ለኢትዮጵያ 250 ቬንቲሌተሮችን መለገሱን አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አስታውቋል።

    ሚያዚያ ወር ላይ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ጋር ባደረጉት የስልክ ንግግር አሜሪካ ለኢትዮጵያ ቬንቲሌተሮችን እንደምትለግስ ቃል ገብተው ነበር።

    በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማይክል ራይኖር ለጤና ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ከበደ ቬንትሌተሮቹን አስረክበዋል።

    ዶ/ር ሊያም መሳሪያዎችን በተረከቡበት ወቅት ለአሜሪካ መንግሥት እና ህዝብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

  7. የስሪ ላንካ ምርጫና ኮሮናቫይረስ

    ስሪ ላንክ

    ስሪ ላንካ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ተራዝሞ የነበረውን የሕዝብ እንደራሴዎች ምርጫ እያከናወነች ነው።

    በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የዋና ከተማዋ ኮሎምቦ ነዋሪዎች ከንጋት ጀምሮ ወደ ምርጫ ጣብያዎች በመሄድ ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

    የቢቢሲዋ አይሻ ፔሬራ የምርጫ ኮሚሽን ሰዎች መራጮች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲመርጡ በቂ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተመክቻለሁ ትላለች።

    ለመምረጥ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ ግዴታ ነው። አልፎም መራጮች የራሳቸውን እስክርቢቶ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል። የምርጫ ጣብያ ሰዎች በየሥፍራው ሳኒታይዘሮች አስቀምጠዋል።

    ድምፅ የመስጠት ሂደቱ ከጥቂት ደቂቃዎች በላይ እንደማይወስድ አይሻ ትናገራለች።

    ስሪ ላንካ እስከዛሬ ድረስ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ የተያዙ ሰዎች 2834 መሆናቸውን ይፋ አድርጋለች። 11 ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸውን አጥተዋል።

  8. ከሙስናው ቅሌት በኋላ የዚምባብዌ ምክትል ፕሬዝደንት የጤና ሚንስትር ሆኑ

    AFP

    የፎቶው ባለመብት, AFP

    የዚምባብዌው ምክትል ፕሬዝደንት ኮንስታንቲኖ ቺዌጋ የአገሪቱ የጤና ሚንስትር ሆነው ተሾሙ።

    የቺዌጋ ሹመት የመጣው ከአንድ ወር በፊት የአገሪቱ ጤና ሚንስቴር በኮሮናቫይረስ መመርመሪያ እና መከላከያ ቁስ ግዢ የተፈጸመው የሙስና ቅሌት ከተጋለጠ በኋላ ነው።

    የቀድሞ የጤና ሚንስትሩ አባዲሃ ሞዮ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያ እና የጤና ባሙያዎች መገልገያ ቁሶች የግዢ ስርዓትን ባልተከተለ መልኩ መቀመጫውን ሃንጋሪ ካደረገ ኩባንያ እንዲገዛ ተደርጓል በሚል ከሳምንታት በፊት ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

    ሞዮ ፍርድ ቤት በቀረቡበት ወቅት 20 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዲገዛ ፈቅደዋል ተብለዋል።

    የቀድሞ ጤና ሚንስትር ጉዳያቸውን ከውጪ ሆነው እንዲከታተሉ በዋስ ከእስር ተለቀዋል።

    አሁን የተሾሙት የጤና ሚንስትር ሮበርት ሙጋቤ ከስልጣን እንዲወርዱ ያደረጉት የጦር መሪ ነበሩ።

    ዚምባብዌ እስካሁን ድረስ ከ4200 በላይ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን የመዘገበች ሲሆን 81 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።

  9. ኮሮናቫይረስ የሴቶችን ሕይወት እየቀየረው ይሆን?

  10. የቴኒስ ኮከቡ ናዳል ወደ አሜሪካ አልሄድም ብሏል

    ናዳል

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ስፔናዊው የሜዳ ቴኒስ ኮከቡ ራፋዔል ናዳል በዩኤስ ኦፕን የሜዳ ቴኒስ ጨዋታ ላይ እንደማይሳተፍ ይፋ አድርጓል።

    ተጨዋቹ ወደ አሜሪካ ላለመሄድ የወሰነው ሃገሪቱ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በቁጥጥር ሥር ማዋል አልቻለችም በሚል ምክንያት ነው።

    የ34 ዓመቱ የዓለም ቁጥር 2 የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ናዳል ከያዝነው ወር ማብቂያ ጀምሮ በኒው ዮርክ የሚካሄደው ውደድር ያመልጠዋል።

    ናዳል የአምናው ዩኤስ ኦፕን ውድድር አሸናፊ ነው።

    የሰርቢያ ኖቫክ ጆኮቪችና አሜሪካዊቷ ሴሬና ዊሊያምስ በውድድሩ ላይ እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

  11. እንኳን በሰላም ወደ ገፃችን መጣችሁ!

    ኮሮና

    በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ የተያዙት ሰዎች ቁጥር ወደ 20 ሺህ እየተጠጋ ነው። የሟቾች ቁጥርም ከ340 በላይ ሆኗል።

    ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች አጠቃላይ ቁጥርም 7 ሺህ 931 መሆኑን ከጤና ሚኒስቴር መረጃ መረዳት ይቻላል።

    በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል የምንኖር የቢቢሲ አማርኛ ቤተሰቦች የሆንን ሁሉ ራሳችንንም ሆነ ወዳጆቻችንን ለኮሮናቫይረስ ላለማጋለጥ አካላዊ ርቀታችንን መጠበቅ፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማድረግና እጃችንን በውሃና በሳሙና በሚገባ መታጠብ እንዳለብን አንርሳ።

    ከኮሮናቫይረስ ጋር የተያያዙ ዋና ዋና መረጃዎችን በዚህ የቀጥታ ዘገባ ገፃችን ላይ እናቀርብላችኋለን።

  12. በኢትዮጵያ ተጨማሪ 588 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ፤ የሰባት ሰዎች ሕይወት አለፈ

    ግራፊክስ

    በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 8201 የላብራቶሪ ምርመራ 588 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴርና የሕብረተሰብ ጤና ተቋም በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

    በዚህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 19 ሺህ 877 ደርሷል።

    በበሽታው ተጨማሪ ሰባት ሰዎች ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን ይህም የሟቾቹን ቁጥር 343 አድርሶታል።

    309 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን እስካሁን 8ሺህ 240 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን መግለጫው አመልክቷል።

    ኢትዮጵያ እስካሁን 452 ሺህ 427 ናሙናዎች ላይ ምርመራ አካሂዳለች።

  13. የውጭ አገር ተጓዦች የኮቪድ-19 ምርመራ ለማድረግ ፈተና ሆኖባቸዋል

  14. ግዙፉ የቢራ ፋብሪካ ያቀደውን የ143 ሚሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት ሰረዘ

    ቢራ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የደቡብ አፍሪካው ግዙፉ የቢራ ፋብሪካ በአገሪቷ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ሲባል የአልኮል መጠጥ መታገዱን ተከትሎ ገቢው በመቀነሱ ሊሰራው አቅዶት የነበረውን የ143 ሚሊየን ዶላር የመሰረተ ልማት ግንባታ መሰረዙን አስታወቀ።

    አገሪቷ የአልኮል መጠጥን ያገደችው ከሦስት ወራት በፊት ነበር።

    የቢራ ፋብሪካ ከሚያመርታቸው ምርቶች መካከል በድዋይዘር፣ ቤክስ፣ ሌፌ፣ ካርሊንግ እና ካስትል ይጠቀሳሉ።

    የድርጅቱ ምክትል የፋይናንስ ፕሬዝደንት አንድሪው ሙራይ “ድርጅቱ እቅዱን የሰረዘው 12 የሥራ ሳምንታት ባለመስራቱ ሲሆን፤ ይህም ከዓመታዊ ምርቱ 30 በመቶ ጋር ይስተካከላል” ብለዋል።

    በሌላ በኩል የደቡብ አፍሪካ ዶክተሮች በበኩላቸው በሕክምና ቦታዎች ከአልኮል ጋር ተያይዘው የሚመጡ የጤና ችግሮችን ለመቀነስ የአልኮል መጠጥ ሽያጭ እንዲታገድ ጠይቀዋል። ምክንያታቸው ደግሞ ያላቸውን አቅም ኮሮናቫይረስን በመከላከል ላይ ለማዋል የሚል ነው።

    ይሁን እንጂ የመጠጥ ኢንዱስትሪው ላይ የተሰማሩ ደግሞ የተጣለው እገዳ እንዲነሳ እያግባቡ ነው።

    ሌላኛው ቢራ አምራቹ ሄኒከን ለ400 ሰዎች የሥራ እድል ሊፈጥር የሚችል ኢንቨስትመንቱን እንዳቆመ Fin24 የተባለ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።

  15. በደቡብ ሱዳን 78 የጤና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ሲያዙ የአንዱ ሕይወት አለፈ

    የጤና ባለሙያ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በደቡብ ሱዳን 78 የሚሆኑ ግንባር ቀደም የጤና ባለሙያዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን የአገሪቷ ጤና ሚኒስተር አስታወቀ።

    እንደ ጤና ባለሥልጣኑ ከሆነ አንድ የጤና ባለሙያም በበሽታው ሳቢያ ሕይወቱ አልፏል።

    የጤና ባለሙያው በጁባ ቲቺንግ ሆስፒታል ይሰራ የነበረ ሲሆን በቫይረሱ ሳቢያ ሕይወቱ ያለፈ የመጀመሪያው የጤና ባለሙያ እንደሆነም የጤና ሚኒስትሩ ዶክተር ማቴው ቱት ለጋዜጠኖች ተናግረዋል።

    ባለፈው ወር ስምንት የጤና ባለሙያዎች 'በሽታውን አምጥታችሁ ቤተሰባችንን ትበክላላችሁ' በሚል ከቤተሰባቸው በደረሰባቸው ተፅዕኖ ሥራቸውን ለቀዋል።

  16. ለሩሲያ የኮቪድ-19 ክትባት የዓለም ጤና ድርጅት ማስጠንቀቂያ ሰጠ

    የክትባት መርፌ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ሩሲያ የኮቪድ-19 ክትባትን በመጭው ጥቅምት ወር ልጀምር እችላለሁ ማለቷን ተከትሎ የዓለም ጤና ድርጅት ሩሲያ ክትባቱን ለማምረት ዓለም አቀፍ መመሪያዎችን መከተል እንዳለባት አስጠነቀቀ።

    የድርጅቱ ቃል አቀባይ ክርስቲያን ሊንድሜር “አንዳንድ ጊዜ ተመራማሪዎች የሆነ ነገር እንዳገኙ ያስታውቃሉ። በእርግጥ ይህ መልካም ዜና ነው፤ ነገር ግን ክትባቱን ለማግኘት ፍንጭ ማግኘት እና በሁሉም የክትባት ደረጃዎች ማለፍ ትልቅ ልዩነት አለው” ሲሉ አስገንዝበዋል።

    የሩሲያ መንግሥት ለዜጎቹ ክትባት ለመስጠት እየተዘጋጀ መሆኑን ያስታወቀው ባለፈው ሳምንት ነበር።

    ይሁን እንጂ የሩሲያ ክትባት በዓለም ጤና ድርጅት ከተመዘገቡና ሦስተኛ ደረጃ ክሊኒካል ሙከራ ላይ ከሚገኙ አንዲሁም በስፋት በሰዎች ላይ እየተሞከሩ ካሉ ስድስት ክትባቶች ዝርዝር ውስጥ የተካተተ አይደለም።

  17. በላቲን አሜሪካ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ5 ሚሊየን አለፈ

    ፀረ ተህዋሲያን የሚረጭ ግለሰብ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    በላቲን አሜሪካ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ5 ሚሊየን የተሻገረ ሲሆን ይህም በዓለማችን ክፉኛ በወረርሽኙ የተመታ ቀጠና አድርጎታል።

    በብራዚል የቫይረሱ ሥርጭት አሁንም እየጨመረ ሲሆን እስካሁን ከ2.7 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በቀጠናው ከተመዘገበው ከ200 ሺህ በላይ የሞት ቁጥርም ግማሽ ያህሉ የተመዘገበው በብራዚል ነው።

    ኮሎምቢያ ደግሞ ሌላኛዋ በወረርሽኙ የተመታች አገር ስትሆን ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 11 ሺህ አዲስ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

    ሜክሲኮ፣ ፔሩ እና ቺሊን ጨምሮ ሌሎች አገራት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ ይገኛል።

    ይሁን እንጂ የጤና ባለሥልጣናት በላቲን አሜሪካ ባለው ድህነትና የተጨናነቀ የሕዝብ ብዛት ያላቸው ከተሞች በመኖራቸው የቫይረሱን ሥርጭት ለመቆጣጠር አዳጋች ነው ብለዋል።

  18. የናይጄሪያ አየር መንገድ በርካታ አብራሪዎችን አሰናበተ

    ኤር ፒስ

    የፎቶው ባለመብት, INSTAGRAM/FLYAIRPEACE

    በወረርሽኙ ክፉኛ የተመታው የናይጄሪያ ዋና አየር መንገድ ኤር ፒስ ቢያንስ 70 አብራሪዎችን ከሥራ ገበታቸው ማሰናበቱ ተገለፀ።

    አየር መንገዱ ውሳኔው ያለበትን እዳ ለመክፈልና ሥራውን ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ብሏል።

    ከዚህ ውሳኔ ላይ ከመድረሱ በፊት ሁለት አማራጮች እንደነበሩት የጠቀሰው አየር መንገዱ፤ አንደኛው አብራሪዎቹን ማሰናበት ሌላኛው ደግሞ የቀሩትን ሰራተኞቹን ደሞዝ መቀነስ ወይም ደግሞ ደሞዝ ባለመክፈል ያሉበትን የፋይናንስ ችግሮች መፍታት ነበሩ ብሏል።

    ከእነዚህ ውስጥ አየር መንገዱ የመጀመሪያውን አማራጭ እንደወሰደም አስታውቋል።

    ከጥቂት ሳምንታት በፊት የአየር መንገዱ ኃላፊ አለን ኦንየማ፤ አየር መንገዶች ያጋጠማቸውን የኢኮኖሚ ቀውስ ለመፍታት መንግሥት ለአቪየሽን ዘርፉ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀው ነበር።

    ይሁን እንጂ አየር መንገዶች መንግሥት በወረርሽኙ ሳቢያ የኢኮኖሚ ቀውስ ያጋጠማቸውን የተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለማንሰራራት ከመደበው 6 ቢሊየን ዶላር እቅድ አልተካተቱም።

    የኤር ፒስ ቃል አቀባይ ስታንሊይ ኦሊሳ በሰጡት መግለጫ፤ መጀመሪያ ላይ ከሰራተኞቹ እንደ ደሞዛቸው መጠን ከዜሮ እስከ አርባ በመቶ ድረስ የክፍያ ቅነሳ ማድረጉን አስታውሰው፤ ይህ ግን አየር መንገዱን ካለበት ችግር ለማውጣት በቂ አልነበረም ብለዋል።

    ምንም እንኳን አሁን የአገር ውስጥ በረራ እንደገና ቢጀመርም ካጋጠመው ቀውስ ግን ሊታደገው አይችልም።

    ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር የአቪየሽን ዘርፉ ተዘግቶ በነበረበት ወቅት በናይጄሪያ ኢንዱስትሪው በየወሩ 77 ሚሊየን ዶላር እያጣ እንደነበር ገልጿል።

  19. ከደቡብ ኮሪያው ለይቶ ማቆያ ሁለት የውጪ ዜጎች አመለጡ

    የበሽታ መከላከያ የለበሱ ግለሰቦች አካባቢ ሲያፀዱ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    በሁለት ሳምንታት ውስጥ ከደቡብ ኮሪያ ለይቶ ማቆያ ሁለተኛው የውጪ ዜጋ ማምለጡን የአገሪቱ ፖሊስ አስታወቀ።

    አንድ የቬትናም ዜጋ ኢንቼኦን ከምትሰኝ ከተማ ካመለጠ ከስምንት ሰዓታት በኋላ በመዲናዋ ሶል ተይዟል።

    ቬትናማዊው አምስተኛ ወለል ላይ ከሚገኘው ክፍሉ በመስኮት በኩል ማምለጡ ተነግሯል።

    ከሁለት ሳምንት በፊት ደግሞ ሌላ አሜሪካዊ ከነበረበት የለይቶ ማቆያ ሆቴል ማምለጡን ፖሊስ አስታውቋል።

    በአሁኑ ወቅት ኮሪያዊያንን ጨምሮ ወደ ደቡብ ኮሪያ የሚገቡ መንገደኞች በሙሉ መንግሥት ባዘጋጃቸው የለይቶ ማቆያ ስፍራዎች ለ14 ቀናት እንዲቆዩ ይደረጋሉ።

  20. በሙከራ ላይ ያሉት ክትባቶች ከምን ደርሰው ይሆን?

    ክትባት

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የአሜሪካ ከፍተኛ የተመራማሪዎች ቡድን ለኮቪድ-19 የሚሆን ክትባት በያዝነው ዓመት ለመስራት ተስፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

    ነገር ግን ክትባት የመስራት ሂደቱ ምን ያህል ሊፈጅ ይችላል?

    ቢቢሲ በሰበሰበው መረጃ መሰረት እስካሁን ድረስ 140 የክትባት መድሀኒቶችን ለማምረት ጥረት እየተደረገ ሲሆን ወደ 20 የሚጠጉት ደግሞ በሰዎች ላይ ሙከራ እየተደረገባቸው ነው።

    ከሙከራዎቹ መካከል፡

    • በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ እየተሰራ የሚገኘው የሙከራ ክትባት የሰው ልጆችን በሽታ የመከላከል አቅም ማነቃቃት እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን አስትራዜኔካ ከሚባለው የመድሀኒት አምራች ለዩኬ ብቻ 100 ሚሊየን ክትባቶችን እንዲያመርት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
    • አሜሪካ ውስጥ ግንቦት ላይ በሰዎች የተሞከሩት ክትባቶች ቫይረሱን የመግደል አቅም እንዳላቸው አሳይቷል።
    • አንድ ቻይና ውስጥ የሚገኝ ቡድን ደግሞ ክትባቱ ደህንነቱ የተጠበቀ መሆኑን ማረጋገጥ ችሏል። የቻይና ወታደሮችም እንዲጠቀሙት እየተደረገ ነው።