
የፎቶው ባለመብት, AFP
በኢኳዶር በኮሮናቫይረስ ሳቢያ ሕይወታቸው እንዳለፈ
የተነገረው የ74 ዓመት ሴት በሕይወት ተገኙ።
አዛውንቷ አልባ ማሩሪ የሚኖሩት በኢኳዶር የኮቪድ -19 ማዕከል በሆነችው ጉያቂል ነው።
እንደ አገሪቷ ጋዜጣ ኤል ኮሜርሲዎ ዘገባ፤ አዛውንቷ ማሩሪ ከፍተኛ ትኩሳትና መተንፈስ ችግር
ካጋጠማቸው በኋላ ሆስፒታል የገቡት ባለፈው ወር ነበር።
በዚያው ወር መጨረሻ ላይ መሞታቸው ተነገረ።
ሆስፒታሉም ቤተሰባቸው አስከሬናቸውን ከንክኪ ነፃ ለመሆን በርቀት እንዲያዩ አደረገ።
የእህታቸው ልጅ ጃሜ ሞርላ ሲያየቸው አክስቱ እንደሆኑ አስቦ እንደነበር
ለባለስልጣናት ተናግሯል።
“ፊታቸውን
ለማየት በጣም ፈርቸ ነበር ፤ አንድ ሜትር ከግማሽ ያህል ርቄ ነበር የተመለከትኳቸው፤ ፀጉራቸው ተመሳሳይ ነበር” ሲል ለኤ ኤፍ
ፒ ተናግሯል።
ከዚያም በስርዓቱ መሰረት አስከሬናቸው
እንዲቃጠል ከተደረገ በኋላ የእርሳቸው እንደሆነ የተነገራቸው የአስከሬን አመድ ለቤተሰብ ተላከ።
ይሁን እንጅ በሞት አፋፍ የነበሩት አዛውንት ሀሙስ
እለት ከነቁ በኋላ ወደ ቀልባቸው ተመልሰው ለዶክተሮች ስማቸውን በመንገር እና የስልክ ቁጥር በመስጠት እህታቸው ጋር እንዲደውሉላቸው
ጠየቁ።
ቤተሰብ የማን አስከሬን አመድ በቤታቸው እንደተቀመጠ ባያውቁም በደስታ ከመፈንጠዝ
አላገዳቸውም። አዛውንቷ ማሩሪ በሕይወት ተገኝተዋል።
ይህ ሊሆን የቻለው በሆስፒታል ውስጥ በሰዎች ማንነት
በተፈጠረ መምታት መሆኑ ተገልጿል።
ሆስፒታሉ ከኮሮናቫይረስ ጋር ተያይዞ በነበረው መጨናነቅ ሳቢያ
ስለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ ጠይቋል።
የአዛውንቷ ቤተሰቦች ግን ለተፈጠረው ስህተት እንዲሁም አስክሬን
ላቃጠሉበት ካሳ እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል።
ኢኳዶር በኮሮናቫይረስ ክፉኛ የተጠቃች አገር ናት። በአገሪቷ ከ22 ሺህ በላይ ሰዎች
በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን 600 የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
የ X ይዘትን ይለፉትይዘቱን X ይፈቅዳሉ?ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል።
ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።