ለኡጋንዳ የሕዝብ እንደራሴዎች ኮሮና መከላከል ዘመቻ የተመደበው ገንዘብ ታገደ
የኡጋንዳ ፍርድ ቤት የሕዝብ እንደራሴዎች በተመረጡበት ስፍራ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመዋጋት እንዲረዳቸው በሚል የተመደበላቸውን 2.6 ሚሊዮን ዶላር አገደ።
እያንዳንዱ የሕዝብ ተወካይ 5,300 ዶላር ይቀበላል ተብሎ የነበረ ሲሆን ፤ከዚህ በተጨማሪም በተመረጡበት ስፍራ በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ሲንቀሳቀሱ ለሚጠቀሙበት መኪና ነዳጅና ለሹፌር የሚከፈል አበል ይሰጣቸው ነበር ተብሏል።
ይህ ውሳኔ እንደተሰማ ኡጋንዳውያን ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን 'በኦንላይን' ፊርማ አሰባስበዋል። አክለውም በርካቶቹ የሕዝብ እንደራሴዎች በቤት የመቀመጥ ገደቡ የተነሳ ወደተመረጡበት አካባቢ እንዳልሄዱ ገልፀዋል።
ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት ማክሰኞ እለት ከፍርድ ቤት የተመደበውን ገንዘብ እግድ ማግኘት መቻላቸው ታውቋል።
ይህንን በማስመልከት የአገሪቱ ጋዜጣ ዴይሊ ሞኒተር በትዊተር ገፁ ላይ አስነብቧል።
ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ
















