ዛሬ እየተከበረ ያለው የፈረንጆቹ ገና በፎቶ

ታትሟል

አብዛኛው ዓለማችን ክፍል የሚገኙ ክርስቲያኖች የፈረንጆቹ ገናን በማክበር ላይ ይገኛሉ። እስቲ በሉ እንዴት እየተከበረ እንደሆነ በፎቶ እናስቃኛችሁ።

ኮሎምቦ ስሪላንካ

የካቶሊክ ሐይማኖት ተከታይ ህጻናት በቅዱስ አንቶኒ ቤተክርስቲያን እንደ መላዕክት ለብሰው ይታያል።

የፎቶው ባለመብት, EPA

የካቶሊክ ሐይማኖት ተከታይ ህጻናት በቅዱስ አንቶኒ ቤተክርስቲያን እንደ መላዕክት ለብሰው ይታያል። በያዝነው ዓመት በዚሁ ቤተክርስቲያን ላይ በተፈጸመ ጥቃት 54 ሰዎች ተገድለዋል።

አቡ ዳቢ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች

አንዲት አማኝ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሻማ ስትለኩስ።

የፎቶው ባለመብት, EPA

አንዲት አማኝ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሻማ ስትለኩስ። በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በርካታ የካቶሊክ እምነት ተከታዮች ሲኖሩ 5 በመቶ የሚሆኑት የፊሊፒንስ ዜጎች ናቸው።

ሃኖይ ቪዬትናም

አንዲት የአገሬው ዜጋ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በዋና ከተማዋ በተሰራው የቅዱስ ዮሴፍ ካቴድራል አጠገብ በሞባይሏ እራሷን ፎቶ ስታነሳ።

የፎቶው ባለመብት, AFP

አንዲት የአገሬው ዜጋ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በዋና ከተማዋ በተሰራው የቅዱስ ዮሴፍ ካቴድራል አጠገብ በሞባይሏ እራሷን ፎቶ ስታነሳ።

ፓሪስ ፈረንሳይ

በፈረንሳይ የ200 ዓመታት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የገና በዓል ሥነ ሥርዓት በኖትርዳም ካቴድራል አልተካሄደም።

የፎቶው ባለመብት, EPA

በፈረንሳይ የ200 ዓመታት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የገና በዓል ሥነ ሥርዓት በኖትርዳም ካቴድራል አልተካሄደም። ምክንያቱ ደግሞ ባለፈው ሚያዝያ ወር በካቴድራሉ ላይ ከባድ እሳት አደጋ ስላጋጠመው ነው።

ናይሮቢኬንያ

በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ፎርት ጂሰስ በሚባለው አካባቢ ሐይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ተደርጓል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ፎርት ጂሰስ በሚባለው አካባቢ ሐይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ተደርጓል።

ቤተልሄም ፍልስጤም ግዛት

በርካታ ሰዎች ዌስት ባንክ በሚገኘውና በመጽሐፍ ቅዱስ እየሱስ ተወልዶበታል በተባለው ቦታ ተሰብስበው በዓሉን አክብረዋል።

የፎቶው ባለመብት, EPA

በርካታ ሰዎች ዌስት ባንክ በሚገኘውና በመጽሐፍ ቅዱስ እየሱስ ተወልዶበታል በተባለው ቦታ ተሰብስበው በዓሉን አክብረዋል።

ቫቲካን

አቡነ ፍራንሲስ ለሰባተኛ ጊዜ ባስተላለፉት የገና በዓል መልእክት ''ፈጣሪ በጣም መጥፎ የሆንነውን እንኳን ይወደናል'' ሲሉ ተደምጠዋል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

አቡነ ፍራንሲስ ለሰባተኛ ጊዜ ባስተላለፉት የገና በዓል መልእክት ''ፈጣሪ በጣም መጥፎ የሆንነውን እንኳን ይወደናል'' ሲሉ ተደምጠዋል።

ሲድኒአውስትራሊያ

የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ሀገሪቱ በእሳት እየተቃጠለች ባለችበት ወቅት ወደ ሃዋይ ለመዝናናት መሄዳቸው ዜጎችን አስቆጥቷል። ቁጣቸውንም በተለያዩ መንገዶች እየገለጹ ነው።

የፎቶው ባለመብት, EPA

የአውስትራሊያው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ሀገሪቱ በእሳት እየተቃጠለች ባለችበት ወቅት ወደ ሃዋይ ለመዝናናት መሄዳቸው ዜጎችን አስቆጥቷል። ቁጣቸውንም በተለያዩ መንገዶች እየገለጹ ነው።