የዩክሬን ባለሥልጣን ሩሲያ በኪዬቭ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሟን ገለጹ
የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደማይሮ ኩሌባ ሩሲያ በዩክሬን መዲና ኪዬቭ ላይ ‘አስከፊ’ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሟን አስታወቁ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ናዚ ጀርመን በዩክሬን ላይ ካደረገው ጥቃት ጋር አነጻጽረውታል።
ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ
በኪዬቭ ያለው የቢቢሲ ዘጋቢ ፖል አደምስ የአደጋ ማስጠንቀቂያ ደወል እና ቢያንስ አንድ የፍንዳታ ድምጽ በከተማዋ መስማቱን ተናግሯል።
አንድ የዩክሬን ጋዜጣ የሩሲያ ታንኮች ወደ መዲናዋ እንዳይገቡ የዩክሬን ወታደሮች በኪዬቭ አቅራቢያ የሚገኝ ድልድይ ማፍረሳቸውን ዘግቧል።




















