አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው ሥልጣን በመረከባቸው ላይ ስጋት እንደነበራቸው ተነገረ
የኢራን የቀድሞ የጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው እርሳቸውን ስለመተካታቸው ጥርጣሬ እንደነበራቸው የአሜሪካ ደኅንነት መረጃ እንደነበረው ምንጮች ለቢቢሲ የአሜሪካ የሚዲያ አጋር ሲቢኤስ ኒውስ ተናገሩ።
መረጃው ኻሜኒ ልጃቸው ሞጅታባ ኻሜኒ “ብቃት እንደሌለው” እና ለመሪነት “ብሩህ አይደለም” ተብሎ ስለሚታሰብ ሥልጣን መረከቡ ላይ ስጋት ነበራቸው ተብሏል።
በተጨማሪም ሟቹ የበላይ መሪ ልጃቸው "በግል ሕይወቱ ውስጥ ችግሮች እንዳሉበት" እንደሚያውቁ ተጠቅሷል።
ሲቢኤስ እንደዘገበው መረጃው አስቀድሞ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና "በዙሪያቸው ላሉ ጥቂት ሰዎች” ደርሷል።
የ56 ዓመቱ አያቶላህ ሞጅታባ ኻሜኒ ከአንድ ሳምንት በፊት የኢራን የበላይ መሪ እንዲሆኑ መመረጣቸው ይታወሳል።