የምርጫ ጣቢያዎች ተዘጉ፤ ዲሞክራቶች በፍራቻ ላይ ሲሆኑ ሪፐብሊካን ደስታቸውን እየገለጹ ነው

የፎቶው ባለመብት, Reuters
በአሜሪካ የመጨረሻዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች በአላስካ እና ሃዋይ ሲዘጉ እስካሁን ባሉ የቆጠራ ውጤቶች ዲሞክራቶች በፍራቻ ላይ ሲሆኑ ሪፐብሊካን ደስታቸውን እየገለጹ ነው።
እስካሁን ባሉ የቆጠራ ውጤቶችን መሰረት ባደረጉ ትንበያዎች መሰረት ዶናልድ ትራምፕ 246 ኢሌክቶራል ኮሌጅ ድምጾችን እንዳገኙ ሲገመት የዲሞክራቷ ካማላ ሃሪስ ደግሞ 194 ኢሌክቶራል ኮሌጅ እንዳገኙ ይታመናል።አንድእጩ ዋይትሃውስን ለማሸነፍ 270 ኢሌክቶራልኮሌጅ ማግኘትአለበት።
እስካሁን ድረስ በአሜሪካ ምርጫ ወሳኝ ከሚባሉት ውስጥ የሰሜን ካሮላይና እና ጆርጂያ ግዛቶችን ትራምፕ ማሸነፍ ችለዋል። እስካሁን ድረስ የአምስት ተጨማሪ ወሳኝ ግዛቶች ውጤት ባይታወቅም ቀደምት ትንበያዎች ትራምፕ በሁሉም እየመሩ እንደሆነ አሳይተዋል።.እነዚህስፍራዎች ካማላሃሪስ ወይምትራምፕ ሊያሸንፉባቸው የሚችሉ ተለዋዋጭነት ያላቸው ሲሆን የምርጫ ውጤቱንም የሚወስኑ እንደሆነ ተነግሯል።
የዲሞክራት ደጋፊዎች እና የምርጫው ስትራቴጂስቶች “ተስፋ የመቁረጥ ስሜት” እየተሰማቸው እንደሆነ ለቢቢሲው የምርጫ ዘጋቢ ተናግረዋል። በፍሎሪዳ የትራምፕ መቀመጫ ደግሞ ከፍተኛ ደስታ እየተገለጸ እንደሆነ ተዘግቧል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የፎቶው ባለመብት, Reuters
























