ተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የፅ/ቤት ኃላፊ ሾሙ

በዘንድሮው የአሜሪካ ምርጫ 47ኛ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ወደ ዋይት ሐውስ ከመመለሳቸው በፊት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቻቸውን ለመሾም ተዘጋጅተዋል። ተሰናባቹ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን በበኩላቸው ያልተቋጩ ሥራዎችን ጨርሰው ሥልጣናቸውን እንደሚያስረክቡ አስታውቀዋል። ትራምፕ የዋይት ሐውስ ፅ/ቤት ኃላፊ ሹመዋል። ቢቢሲ አማርኛ የአሜሪካ ምርጫ ሂደትን የተመለከቱ ዘገባዎች በዚህ ገጽ በቀጥታ ያቀርባል።

ጭምቅ ሃሳብ

  • ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ
  • የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ለትራምፕ ‘የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት’ አስተላለፉ
  • ትራምፕ “አስደናቂ ድል ተቀዳጀሁ” አሉ
  • ትራምፕ ፕሬዝዳንት ለመሆን ሲቃረቡ፣ ሪፐብሊካኖች በሁለቱም ምክር ቤቶች የበላይነት እየያዙ ነው
  • ሪፐብሊካኖች የህግ መወሰኛ ምክር ቤቱን ይቆጣጠራሉ- ትንበያ
  • የምርጫ ጣቢያዎች ተዘጉ፤ ዲሞክራቶች በፍራቻ ላይ ሲሆኑ ሪፐብሊካን ደስታቸውን እየገለጹ ነው
  • ትራምፕ ወሳኝ የምትባለውን የሰሜን ካሮላይና ግዛትን አሸነፉ
  • የአሜሪካዊ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ውጤት እንደ ሩሲያ እና ቻይና ላሉ ኃያላን ሀገራት ምን ይፈይዳል?
  • የፕሬዚዳንታዊ እጩዎቹ የምርጫ ዘመቻ በእምነት ላይ የተመሰረተ ነው?
  • የአይዋ ግዛት ለምን የትኩረት ማዕከል ሆነች?
  • “የጋዛን ጦርነት ለማስቆም የተቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ” ካማላ ሃሪስ
  • ከምርጫው ቀን በፊት ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ድምጽ ሰጥቷል
  • እስካሁን ባለው ሂደት ከ78 ሚሊዮን በላይ አሜሪካውያን ድምጻቸውን የሰጡ ሲሆን ይህም ከአራት ዓመት በፊት የነበረውን የመጀመሪያ መራጮች ተሳትፎ ክብረ ወሰን የሰበረ ነው

የቀጥታ ሽፋን

  1. ስደተኞች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ባይገቡ ኖሮ አሜሪካ ምን ትመስል ነበር?

    የአሜሪካ ቪዛ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    እየተካሄደ ባለው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ፉክክር በአገሪቱ የሚገኙ ስደተኞች ዋነኛ ጉዳይ የምረጫ ቅስቀሳቸው ዋነኛው ርዕሰ ጉዳይ ነው።

    የሪፐብሊካን እና የዴሞክራቲክ ፓርቲዎች ዕጩ ተወዳዳሪዎች ወደ አሜሪካ በተለይም በሜክሲኮ ድንበር በኩል በሚገቡት ስደተኞቸ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ።

    ዶናልድ ትራምፕ ስለ ስደተኞች ጉዳይ አሳሳቢነት ሲያወሱ ክስተቱን ከ“ወረራ” ጋር በማመሳሰል ነው ደጋግመው የሚያስጠነቀቁት። ተመርጠው ወደ ሥልጣን የሚመለሱ ከሆነም ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸውን ስደተኞች በጅምላ ለማባረርም አየዛቱ ነወ።

    የዲሞክራቷ ተቀናቃኛቸው ካማላ ሃሪስ በበኩላቸው የቀድሞውን ፕሬዚዳንት በስደተኞች ዙሪያ “ፍርሃት እና መከፋፈል እያቀጣጠሉ ነው” ሲሉ ከሰዋቸዋል።Link

  2. በአሜሪካ ምርጫ እስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን ማንን ይደግፋሉ? ትራምፕን ወይስ ካማላ?

    ኔታንያሁ እና ካማላ ሃሪስ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ዶናልድ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው ሲመረጡ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ደስታቸውን ለመግለፅ አንድ መንደር በስማቸው ሰየሙ።

    ትራምፕ ሃይትስ በጎላን ተራሮች አካባቢ የሚገኙ ድንጋያማ እና በማዕድን የተሞላ ሥፍራ ነው።

    ትራምፕ የጎላን ተራሮች ያሉበትን ቦታ የእስራኤል ነው ብለው ዕውቅና ሰጡ። በግማሽ ምዕተ ዓመት ይህ ያደረጉ የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ናቸው።

    ጎላን በአውሮፓውያኑ 1967 ጦርነት ከሶሪያ የተወሰደ መሬት ሲሆን፣ በኋላ የእስራኤል ክፍል ሊሆን ችሏል።

    በዚህ ሥፍራ የሚኖሩ ሰዎች ቁጥራቸው ትንሽ ነው። ከሁለት ደርዘን አይበልጥም። ወታደሮችም በአካባቢው ይኖራሉ።

    ሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ አሊያም ዲሞክራቷ ተቀናቃኛቸው ካማላ ሃሪስ መመረጣቸው ለቀጣናው ሀገራት ምን ትርጉም አለው?Link

  3. ካማላ ሀሪስ እና ዶናልድ ትራምፕ ፕሬዝደንት ለመሆን የትኞቹን ግዛቶች ማሸነፍ አለባቸው?

    የአሜሪካ ካርታ እና የምርጫ ሳጥን

    አሜሪካ 50 ግዛቶች አሏት። ሁለቱ አውራ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን እኒህን ግዛቶች ተቀራጭተዋቸዋል። ይህ ማለት የትኛው ግዛት ለየትኛው ፓርቲ ድምፁን እንደሚሰጥ ይታወቃል ማለት ነው።

    ነገር ግን ሰባት ግዛቶች ለየትኛው ፓርቲ ድምፃቸውን እንደሚሰጡ አይታወቅም። ለዚህ ነው ወላዋይ የሚባሉት።

    እኒህ ግዛቶች ኔቫዳ፣ አሪዞና፣ ኖርዝ ካሮላይና፣ ጆርጂያ፣ ዊስኮንሲን፣ ሚሺጋን እና ፔንሲልቬኒያ ናቸው።

    በአሜሪካ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ዕጩዎች በርካታ ድምፅ ስላገኙ መንበረ-ሥልጣኑን ማግኘት ይችላሉ ማለት አይደለም።

    ሁለቱ ዕጩዎች የሚፎካከሩት በ50ዎቹ ግዛቶች የሚደረጉትን ምርጫዎች ለማሸነፍ ነው የሚታገሉት።

    እያንዳንዱ ግዛት ኢሌክቶራል ኮሌጅ የሚባል ቁጥር አለው። ይህ የሚሆነው በሕዝብ ቁጥር ብዛት ላይ ተመስርቶ ነው። በአጠቃላይ 538 ኢሌክቶራል ኮሌጆች አሉ። ዕጩዎቹ ከእነዚህ መካከል 270 እና ከዚያ በላይ ማግኘት አለበባቸው።

    ይህ እንዲሆን ደግሞ ከሰባቱ ወሳኝ ግዛቶች ቢያንስ በሶስቱ ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል።

  4. የአነጋጋሪው ዶናልድ ትራምፕ የሕይወት ታሪክ - ከሪል ስቴት እስከ ፖለቲካ

    የቀድሞው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ለመሆን የተወዳደሩት በአውሮፓውያኑ 2016 ነው። ነገር ግን በኒው ዮርክ ግዙፍ የሪል ስቴት ኩባንያ ባለቤት የሆኑትን ባለሀብት ከዚያም በፊትም የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ትኩረት ነፍገዋቸው አያውቁም።

  5. ካማላ ሀሪስ በአዮዋ ግዛት እየመሩ ነው

    ዕጩ ፕሬዝደንት ካማላ ሀሪስ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    ከአዮዋ ግዛት የወጣ ቅድመ ትንበያ እንደሚያሳየው ዕጩ ፕሬዝደንት ካማላ ሀሪስ በ47 በመቶ ሲመሩ ዶናልድ ትራምፕ በ44 በመቶ ይከተላሉ።

    አን ሴልዘር የተባለው ታዋቂ ድምፅ ሰብሳቢ ሴቶች እና ገለልተኛ መራጮች ድምፃቸውን ለካማላ እንደሚሰጡ ከ808 መራጮች ባገኘው መረጃ ማጣራቱን አሳውቋል። ነገር ግን ይህ የመጨረሻውን ድምፅ ያሳያል ማለት እንዳለሆነ ድርጅቱ አሳውቋል።

    ድርጅቱ ለቢቢሲ እንደተናገረው ሁለቱም ዕጩዎች 50 በመቶ ድምፅ ባለማምጣታቸው ማክሰኞ በምርጫው ቀን ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማወቅ ከባድ ነው።

    ዶናልድ ትራምፕ ባለፉት ሁለት ምርጫ በአዮዋ ግዛት ከ10 በመቶ በላይ በሆነ ድምፅ ነው ያሸነፉት። አዮዋ ከሰባቱ ወሳኝ እና ወላዋይ ከሚባሉ ግዛቶች አንዷ አይደለችም። ለወትሮው ሪፐብሊካን ናት በምትባለው ግዛት ሁለቱ ዕጩዎች ተቀራራቢ ሆነው መገኘታቸው ግን ጉዳዩ መነጋገሪያ እንዲሆን አድርጎታል።

    አሜሪካ በምትከተለው ኢሌክቶራል ኮሌጅ በተባለ ሥርዓት ምክንያት በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ ዕጩ ሊረታ ይችላል። በጠቅላላው 538 ኢሌክቶራል ኮሌጆች አሉ። እያንዳንዱ ግዛት እንደ ሕዝብ ብዛቱ ይሰጠዋል። ሀሪስ አሊያም ትራምፕ ወደ ዋይት ሐውስ ለመግባት ቢያንስ 270 ኢሌክቶራል ኮሌጅ ማግኘት አለባቸው።

    አዮዋ 6 ኢሌክቶራል ኮሌጅ አላት። ነገር ግን ግዛቷ ወሳኝ ከሚባሉት ዊስኮንሲን እና ሚሺጋን ጋር ተመሳሳይነት አላት።

    የካማላ ሀሪስ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን ካማላ በአዮዋ ግዛት እየመሩ መሆናቸውን ተከትሎ ደስታቸውን ሲገልጡ የትራምፕ የቅስቀሳ ቡድን ግን ጉዳዩን እያስተባበለው ይገኛል።

    የትራምፕ የምርጫ ዘመቻ ቡድን ቃል አቀባይ የሆኑት ጄሰን ሚለር በእያንዳንዱ ምርጫ አንድ “የማይረባ ድምፅ ሰብሳቢ” አይጠፋም ብለው ኤመርሰን የሚባለውን ድምፅ ሰብሳቢ ዋቢ በማድረግ ትራምፕ በአዮዋ ግዛት በ10 በመቶ እየመሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

  6. ከምርጫው በፊት ባለው ቅዳሜ ምን ተከሰተ?

    ዶናልድ ትራምፕ ወላዋይ ከሚባሉት ግዛቶች አንዷ በሆነችው ኖርዝ ካሮላይና እና በቨርጂኒያ ግዛት ቅስቀሳ አድርገዋል። ትራምፕ ትኩረታቸውን ምጣኔ ሀብት እና ስደት ላይ አድርገው ነው ንግግር ያሰሙት።

    የቀድሞው ፕሬዝደንት በሕክምና ፆታ ስለሚቀይሩ ግለሰቦችም (ትራንስጀንደርስ) ንግግር አድርገዋል። “የወላጆችን መብት” እጠብቃለሁ ብለው “ወንዶች ከሴቶች ስፖርት ራሳቸውን እንዲያርቁ” አስጠንቅቀዋል።

    ዕጩው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    በሌላ በኩል ካማላ ሀሪስ ቀናቸውን የጀመሩት አትላንታ ሲሆን ቀጥለው ወደ ኖርዝ ካሮላይና። ዲሞክራቷ ዕጩ ጆርጂያ በነበራቸው ቆይታ ስለሴቶች የመውለድ መብት ትኩረት አድርገው ንግግር ያሰሙ ሲሆን ትራምፕ “መብታችሁን ያግዳል” የሚል ማስጠንቀቂያ አሰምተዋል።

    ዕጩ ምክትል ፕሬዝደንቶችም እንዲሁ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ውለዋል። ሪፐብሊካኑ ጄዲ ቫንስ ዲሞክራቱ ቲም ዋልዝ በአሪዞና ግዛት ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ነው የዋሉት።

    ዕጩዎቹ እሑድ በተለያዩ ግዛቶች እና ከተማዎች ተዘዋውረው ቅስቀሳ ለማድረግ ዕቅድ ይዘዋል።

    የካማላ ሀሪስ የቅስቀሳ ፖስተር
  7. ዶናልድት ትራምፕ - “የድላችን ቀን የነፃነት ቀን ይሆናል”

    ዕጩው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, REUTERS

    በኖርዝ ካሮላይና ግዛት ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩት ትራምፕ ደጋፊዎቻቸው በጊዜ ወጥተው ድምፃቸውን እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

    “በሰፊ ልዩነት ስናሸንፍ በጠባቡ መሸነፋችን አይቀርም” ብለዋል ትራምፕ።

    የቀድሞው ፕሬዝደንት አክለው “ዩናይትድ ስቴትስ አሁን በቁጥጥር ሥር ያለች ሀገር ናት። ከዚህ ቀንበር ነፃ የምንወጣበት ቀን በጣም ቅርብ ነው” ብለዋል።

    ትራምፕ ማክሰኞ ጥቅምት 26 የሚደረገው ምርጫ “በአሜሪካ የነፃነት ቀን ይሆናል። ነፃነት ይሰፍናል” ሲሉ ተደምጠዋል።

    ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻዎቹ ሁለት የምርጫ ቅስቀሳ ቀናት በተለያዩ ግዛቶች እየተዘዋወሩ ደጋፊዎቻቸውን ለመቀስቀስ አስበዋል። እሑድ በሶስት ቦታዎች ተዘዋውረው ቅስቀሳ ለማድረግ፤ ሰኞ ዕለት ደግሞ አራት ሥፍራዎችን ለማዳረስ አቅደዋል።

    “እንዲህ ጠንክሬ የምሠራው ማሸነፍ ስላለብን ነው” ያሉት ፕሬዝደንቱ ለኖርዝ ካሮላይና ደጋፊዎቻቸው 90 ደቂቃ የፈጀ ንግግር አድርገዋል።

    የቀድሞው ፕሬዝደንት ንግግራቸውን ሲቋጩ “በፍፁም አንወረርም። በፍፁም ቀንበር ውስጥ አንገባም። በፍፁም የሚሉንን እየሰማን አንኖርም። በፍፁም እጅ አንሰጥም” ብለዋል።

    ትራምፕ ከመድረኩ ከመውረዳቸው በፊት ዋይኤምሲኤ በተሰኘው ሙዚቃ ሲደንሱ ታይተዋል።

  8. ከምርጫው ቀን በፊት ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ድምጽ ሰጠ

    ቀድመው ድምጻቸውን ከሰጡ መራጮች መካከል

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የምስሉ መግለጫ, ቀድመው ድምጻቸውን ከሰጡ መራጮች መካከል

    በአሜሪካ የሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ይፋዊ የድምጽ መስጫ ቀን ማክሰኞ ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም. ቢሆንም ባለፉት ቀናት በርካታ አሜሪካውያን ቀድመው ድምጻቸውን መስጠታቸው ተገልጿል።

    የፍሎሪዳ ዩኒቨርስቲ የምርጫ መረጃዎች መከታተያ ማዕከል ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው እስከ ቅዳሜ ጥቅምት 24 ከሰዓት በኋላ ድረስ ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ድምጽ ሰጥቷል።

    ይህ አሃዝ በቀደመው የኮቪድ 19 ስጋት በነበረበት የ2020 ምርጫ ከተመዘገበው 101.5 ሚሊዮን በ30 ሚሊዮን ያነሰ ቢሆንም፣ በ2016 ከነበረው 47.2 ሚሊዮን እና በ2012 ከተሰጠው 46.2 ሚሊዮን የበለጠ ሆኖ በከፍተኛነት ተመዝግቧል።

    ሁለቱ ፕሬዝዳንታዊ ዕጩዎች የዲሞክራቷ ካማላ ሃሪስ እና የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ከምርጫው ቀን በፊት በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ የመጨረሻውን ቅስቀሳቸውን እያካሄዱ ነው።

    ትራምፕ ዛሬ ቅዳሜ ሰሜን ካሮላይና ውስጥ ጋስቶኒያ እና ግሪንስቦሮ እንዲሁም ቨርጂኒያ ሳሌም ውስጥ በተለያዩ ሰዓታት ቅስቀሳ ሲያካሂዱ፤ ካማላ ሐሪስ አትላንታ ጆርጂያ እንዲሁም ሰሜን ካሮሊና ሻርለት ውስጥ በበኩላቸው ለመራጮች ንግግር በማድረግ ቅስቀሳ ያደርጋሉ።

    የመጨረሻ ቅስቀሳ እያካሄዱ ያሉት ሐሪስ እና ትራምፕ

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, የመጨረሻ ቅስቀሳ እያካሄዱ ያሉት ሐሪስ እና ትራምፕ
  9. የዋሺንግተን ግዛት የተወሰኑ የብሔራዊ ጥበቃ አባላቱ በተጠንቀቅ እንዲሆኑ ማዘዙን አስታወቀ

    ሁከት

    የዋሽንግተን ግዛት አስተዳዳሪ የተወሰኑ የብሔራዊ ጥበቃ አባላቱ ከ2024 ምርጫ ጋር በተያያዘ አመጾች ሊቀሰቀሱ ይችላሉ የሚል መረጃ እና ስጋቶች በመኖራቸው በተጠንቀቅ እንዲሆኑ ማዘዛቸውን ገለፁ።

    ይህ ግዛት በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የድምፅ መስጫ ሳጥኖች ከተቃጠሉባቸው ሁለት ግዛቶች መካከል አንዱ ነው።

    "ከ2024 አጠቃላይ ምርጫ ጋር በተገናኘ ሁከት ወይም ሌላ ሕገወጥ ተግባር ሊኖር ይችላል የሚል ጥቅል መረጃ በመኖሩ እንዲሁም ስጋቶችን መሰረት በማድረግ ምላሽ ለመስጠት በሚያስችል መልኩ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናችንን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ" ሲሉ ገዥው ጄይ ኢንስሊ በድረ-ገፃቸው ላይ በፃፉት መልዕክት አስታውቀዋል።

    በቫንኮቨር ከተማ ተቀጣጣይ ነገርን በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ የምርጫ ሳጥኖች ውድመት እንደደረሰባቸው በወቅቱ ተገልጾ ነበር።

    ሰኞ ዕለት በፖርትላንድ ኦሪገን አካባቢ ሁለት የድምጽ መስጫ ሳጥኖች በእሳት ከተቃጠሉ በኋላ ኤፍቢአይ ምርመራ ማድረግ መጀመሩ ተዘግቧል።

    በዋሽንግተን ግዛት ከፖርትላንድ 16 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኝ ትንሽ ከተማ ቫንኮቨር ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ የድምጽ መስጫ ሳጥኖች ናቸው የተቃጠሉት።

    ይህ በእንዲህ እንዳለ በፖርትላንድ ደቡብ ምስራቅ ክፍል ተቀጣጣይ መሳሪያ በምርጫ ሳጥን ውስጥ ተቀምጦ ቃጠሎ በመከሰቱ ሦስት የምርጫ ሳጥኖችን አውድሟል ሲሉ ባለስልጣናት ተናግረዋል።

    ፖሊስ ሰኞ ዕለት ሁለቱ ክስተቶች የተገናኙ መሆናቸውን አስታውቆ ነበር።

  10. ፕሬዝደንታዊ ዕጩዎቹ ከልጅነት እስከ ዕውቀት - ከዚህ ቀደም ያልታዩ የሃሪስ እና የትራምፕ ፎቶዎች

    ሃሪስ እና ትራምፕ በሦስት ዓመታቸው የተነሱት ፎቶ

    የፎቶው ባለመብት, Alamy

    የምስሉ መግለጫ, ሃሪስ እና ትራምፕ በሦስት ዓመታቸው የተነሱት ፎቶ

    የአሜሪካ ምርጫ ሲቃረብ መራጮች በዕጩዎች ፎቶ ይጨናነቃሉ። ዕጩዎች የምርጫ ቅስቀሳ ሲያደርጉ፤ ደጋፊዎቻቸውን ሲጨብጡ፤ አውሮፕላን ሲሳፈሩ እና ሲወርዱ።

    ነገር ግን የብዙዎቹ ዕጩዎች የቀድሞ ፎቶዎች ብዙም ብቅ ሲሉ አይታዩም።

    ከላይ የሚታዩት ዶናልድ ትራምፕ እና ካማላ ሃሪስ ዋይት ሐውስ ምን እንደሆነ እንኳ ሳያውቁ በፊት በሦስት ዓመታቸው የተነሷቸው ፎቶዎች ናቸው።

    እነሆ በርካታ አስርት ዓመታት አልፈው ዲሞክራቷ ዕጩ ፕሬዝደንት ካማላ ሃሪስ እና ዶናልድ ትራምፕ ተፋጠዋል።

    ካማላ ልጅነታቸውን ያሳለፉት በካሊፎርኒያ ግዛት ኦክላንድ ከተማ ነው፤ ትራምፕ ደግሞ በኒው ዮርክ ግዛት ኩዊንስ ነው ያደጉት።

    ሃሪስ እና እህታቸው ማያ የካንሰር ጥናት ባለሙያ እና የማኅበረሰብ አንቂ በሆኑት ሕንዳዊት እናታቸው ሺያማላ ጎፓላን ሃሪስ እንክብካቤ ነው ያደጉት።

    የትራምፕ አባት ፍሬድ ትራምፕ ደግሞ የጀመርን ስደተኞች ልጅ ሲሆኑ፣ እናታቸው ማሪ አን ትራምፕ ደግሞ ስኮትላንድ ነው የተወለዱት።

    ትራምፕ በ13 ዓመታቸው የኒው ዮርክ ወደ ሚገኘው ወታደራዊ አካዳሚ ገብተዋል።Link

  11. ትራምፕ እና ካማላ ሐሪስ በአሜሪካ ምርጫ ወሳኝ ግዛቶችን ድምጽ ለማግኘት እየተፋለሙ ነው

    የአሜሪካ ፕሬዝዳነታዊ ምርጫ ተፎካካሪዎች ካማላ ሐሪስ እና ዶናልድ ትራምፕ

    ሰሜን ካሮላይና የአሜሪካ ቀጣዩ ፕሬዝዳንት ማን እንደሆነ ከሚወስኑ ሰባት ወሳኝ ግዛቶች አንዷ ነች።

    ትራምፕ እና ካማላ ሐሪስ ከመጨረሻው የምርጫ ቀን በፊትየምረጡኝ ቅስቀሳቸውን ለማካሄድ ቅዳሜ ዕለት ወደግዛቲቱ ያመራሉ።

    ግዛቲቱ 10.7 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት ሲሆን አሸናፊው እጩ ከጠቅላላው 538 ውስጥ 16 ኤሌክቶራል ኮሌጅ ያገኛል።

    እኤአ በ202 ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ግዛት 74,000 ድምፅ በማግኘት አሸንፈዋል።

    ዴሞክራቶች ይህንን ለመገልበጥ ከቻሉ የትራምፕ ወደ ኋይት ሀውስ ጉዞ በጣም ከባድይሆናል።

    የግዛቲቱ ጥቁር መራጮች ባለፈው ምርጫ ዲሞክራቶች ግዛቱን እንዲያሸንፉ ትልቅ ምክንያት ነበሩ።

    የካማላ ሐሪስ ጉዞ በዚህ የምረጡን ቅስቀሳ ላይ ያንን መራጭ ሕዝብ ዒላማ አድርጓል።

    ዲሞክራቶች ሰሜን ካሮላይንና ለማሸነፍ ከፍተኛ ጥቁር መራጮች ያስፈልጋቸዋል ይላሉ ባለሙያዎች።

    ለሪፐብሊካኖች የማሸነፍያ ቁልፉ የፓርቲያቸውመራጮች በከፍተኛ ዋጋ መመዝገባቸውን ማረጋገጥ ነው።

    በአሜሪካ ምርጫ ወሳኝ ናቸው የሚባሉት ሰባት ግዛቶች ድምፃቸውን ለማን እንደሚሰጡ እስካሁን አልለየም።

    በእነዚህ ግዛቶች በካማላ እና ትራምፕ መካከል ያለው ልዩነት እጅግ ጠባብ ነው።

    በጣም ብዙ ኢሌክቶራል ኮሌጅ ያላት ፔንሲልቬኒያ ግዛት ናት። በዚህችም ግዛት ቢሆን ማን አሸናፊ ይሆናል የሚለውን መለየት አዳጋች ሆኗል።

    ሰባቱ ወሳኝ ግዛቶች ፔንሲልቬኒያ፣ ሰሜን ካሮላይና፣ ኔቫዳ፣ አሪዞና፣ ጆርጂያ፣ ሚቺጋን እና ዊስኮንሰን ናቸው።

  12. ትራምፕ እና ካማላ ሐሪስ በዊስኮንሰን ግዛት በጥቂት ኪሎሜትሮች ርቀት የምረጡኝ ቅስቀሳ እያካሄዱ ነው

    አሜሪካዊቷ ራፐር ካርዲ ቢ ለካማላ ሐሪስ ያላትን ድጋፍ ገልጻለች

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    የምስሉ መግለጫ, አሜሪካዊቷ ራፐር ካርዲ ቢ ለካማላ ሐሪስ ያላትን ድጋፍ ገልጻለች

    የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወደ ፍጻሜው ሲቃረብ፣ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ሁለቱም እጩዎች አንዱ ከሌላው በጥቂት ማይሎች ርቀት ላይ በመሆን ቅስቀሳ ሲያካሄዱ ነበር።

    ዶናልድ ትራምፕ እና ካማላ ሃሪስ ትናንት ምሽት በወሳኟ ዊስኮንሰን ግዛት በመገኘት የምረጡኝ ቅስቀሳቸውን አድርገዋል።

    "ይህን ግዛት እናሸንፋለን፤ ምርጫውን እናሸንፋለን። በጋራ ሆናችሁ ለካማላ መንገር የእስካሁኑ በቂ አንደሆነ እና ከዚህ በላይ መታገስ እንደማትችሉ መናገር ይኖርባችኋል። እሷ በታሪካችን ካየናቸው በጣም መጥፎዋ ምክትል ፕሬዝዳንት ነች" ሲሉ ትራምፕ በሚልዋኪ ከተማ ለተሰበሰቡት የሪፐብሊካን ደጋፊዎች ተናግረዋል።

    በምዕራብ አሊስ ሙዚቀኛዋ ካርዲ በዲሞክራት መራጮች በተገኙበት ለካማላ ሐሪስ ድጋፏን ሰጥታለች።

    "ለእናንተ እውነቱን መናገር እፈልጋለሁ። በዚህ ዓመት ድምጽ አልሰጥም ነበር። አልመርጥም ነበር። ነገር ግን ካማላ ሐሪስ ውድድሩን ስትቀላቀል ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ አስቀይራኛለች።" ብላለች

  13. የመጀመሪያዋ የአሜሪካ ሴት ፕሬዝዳንት ለመሆን እየተፎካከሩ ያሉት ካማላ ሃሪስ ማን ናቸው?

    ካማላ ሃሪስ

    የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ከዕድሜ መግፋት ጋር በተያያዘ በገጠማቸው አካላዊ እና አእምሯዊ መዳከም ምክንያት በድጋሚ ለመመረጥ ከሚደረገው ፉክክር እንዲወጡ ሲደረግባቸው የነበረውን ጫና በመጨረሻ ተቀብለውታል።

    ባይደን ከምርጫው ለመውጣት መወሰናቸውን ተከትሎ ምክትል ፕሬዚዳንታቸው ካማላ ሃሪስ የዲሞክራቲክ ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ ድጋፋቸውን ገልጸዋል።

    የ59 ዓመቷን የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላን ሃሪስ ለፕሬዝዳንትነት ከዶናልድ ትራምፕ ጋር በሚደረገው ፉክክር የዴሞክራቲክ ፓርቲ ዕጩ እንዲሆኑ ከፓርቲው አባላት ድጋፍን አግኝተዋል።

    ሆኖም ግን የምክትል ፕሬዝዳንቷ የተቀባይነት ደረጃ ዝቅተኛ እንደሆነ የሚነገር ሲሆን፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ባገለገሉበት ወቅትም የአገሪቱ መሪ ሆነው ለመመረጥ ምን ያህል ብቃት አሳይተዋል የሚለው ላይ ጥርጣሬ አለ።Link