የነዳጅ ዋጋ ከኢራን ጦርነት ወዲህ ባልታየ መጠን ቀነሰ

የፎቶው ባለመብት, The Dallas Morning News via Getty Images
መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መጓጓዝ መቀጠላቸውን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ከኢራን ጦርነት ወዲህ ባልታየ መጠን ቀነሰ።
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በበርሜል ወደ 72.48 ዶላር ወርዷል። ይህም አሜሪካ እና እስራኤል ኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩበት ቀን በፊት የነበረው ዋጋ ነው።
ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን በመዝጋቷ ባለፉት ወራት የነዳጅ ዋጋ አሻቅቦ ነበር።
ኢራን እና አሜሪካ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙበት ዕለት አንስቶ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ እያሽቆለቆለ መጥቷል።
የቴህራን እና ዋሽንግተን ልዑካን በስዊትዘርላንድ ውይይት ካደረጉ በኋላ አሜሪካ የኢራን የነዳጅ የወጪ ንግድ ላይ ጥላ የነበረውን ማዕቀብ አላልታለች።
ስምምነት ከተፈራሙ በኋላ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚተላለፉ መርከቦች ቁጥር ጨምሯል።
ድፍድር ነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ እንዲሁም ማዳበሪያ እና ሌሎችም ሸቀጦች የጫኑ መርከቦች እየተላለፉ ይገኛሉ።




















