በጀርመን በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ቡና ቤቶች ይከፈቱ ብለው ሰላማዊ ሰልፍ ወጡ
ጥቂት የማይባሉ በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ሴቶች ቡና ቤቶች ይከፈቱልን በማለት በጀርመኗ ዋና ከተማ በርሊን ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ያደረጉት ሰልፈኞቹ ከጀርመን ፌደራል ምክር ቤት በር ላይ ነው ጥያቄያቸውን ያቀረቡት።
‘’በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ሰዎች ሥራቸው ይወደድም ይጠላ ሊከበሩ ይገባል’’ የሚል መፈክር ሰልፈኞቹ ይዘው የታዩ ሲሆን፤ አንዲት ሴት ደግሞ ቡና ቤቶቹ የማይከፈቱ ከሆን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ሥራቸውን ለመስራት እንደሚገደዱ መልዕክቷን አስተላልፋለች።
ምንም እንኳን ጀርመን እንቅስቃሴ ገደቡን ማላለት ብትጀምርም በኮሮረናቫይረስ ምክንያት የወሲብ ንግድ ዘርፉ አሁንም በእጅጉ ተጎድቷል ተብሏል።
ነገር ግን እንደ ስዊትዘርላንድ፣ ኦስትሪያ እና ኔዘርላንድስ ያሉ ጎረቤት አገራት ቡና ቤቶች እንዲከፈቱ ፈቅደዋል።