የሊባኖስ አየር መንገድ ዳግም በረራ ጀመረ

የፎቶው ባለመብት, Reuters
የሊባኖስ ብቸኛው ዓለም አቀፍ አየር መንገድ ከሶስት ወራት በኋላ ዳግም ተከፈተ።
ለአሁኑ የቤሩት አየር መንገድ ካለው አቅም 10 በመቶ ብቻ የሚጠቀም ሲሆን መንገደኞች የኮቪድ-19 ምርመራ እንደሚያደርጉ ቫይረሱም ከተገኘባቸው በቤታቸው ራሳቸውን ለይተው እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
ከቤሩት የተነሳው የመጀመሪያው አውሮፕላን በአዲስ አበባ አድርጎ ካይሮ፣ ለንደን የሚሄድ መሆኑ ተገልጿል።
ሊባኖስ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እንዳይስፋፋ ለማድረግ የእንቅስቃሴ ገደቦችን ብትጥልም የአገሪቱን ምጣኔ ኃብት ግን እንዲንኮታኮት አድርጎታል።
በቅርብ ወራት ውስጥ የሊባኖስ የገንዘብ ያለውን አቅም 80 በመቶ ማጣቱ ተነግሯል።
በርካታ ሊባኖሳውያንም የሚበላ ለመግዛት መቸገራቸው ተገልጿል።
ሊባኖሳውያን ይህ የምጣኔ ሃብት ድቀት በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት እንዳያባብሰውና በርካታ የተማሩ ሰዎች አገራቸውን ጥለው እንዳይሰደዱ ሰግተዋል።















