ክሮሺያ ድንበሯን ለአስር አገራት ክፍት አደረገች

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ክሮሺያ ድንበሯን ለአስር አገራት መክፈቷን ገለፀች።
ድንበሯን ከከፈተችላቸው አገራት መካከል የቱሪስት ፍሰት ያላቸው ኦስትሪያ፣ ጀርመን እና ቼክ ሪፐብሊክ ይገኙበታል።
ነገር ግን ማንኛውም ጎብኚ ከቫይረሱ ነጻ መሆኑን የሚያሳይ ሰነድ ይዞ መምጣት እንዳለበት ደንግጋለች።
ክሮሺያ በኮሮናቫይረስ ምክንያት 100 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ወረርሽኙን ለመከላከል በፍጥነት ምላሽ መስጠቷ ተገልጿል።
የአገሪቱ ኀብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በታህሳስ ወር ከቻይና ዉሃን ለመጡ ቱሪስቶች አገሪቱ ውስት ከመግባታቸው በፊት መመሪያዎችን በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረጉ ተገልጿል።
የኮሮነቫይረስ ወረርሽኝ የአገሪቱን ዋነኛ የገቢ ምንጭ የሆነውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ጎድቶታል።
ከዛሬ ጀምሮ ከሀንጋሪ፣ ኦስትሪያ፣ ቼክ ሪፐብሊክ፣ ስሎቫኪያ፣ ኢስቶኒያ፣ ላቲቪያ፣ ሊቱዋኒያ፣ ፖላንድና ጀርመን የሚመጡ መንገደኞች እንዲገቡ ተፈቅዷል።


















