በአፍሪካ ስላለው የኮሮናቫይረስ ዘገምተኛ አካሄድ ምን ማለት ይቻላል?

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የኮሮናቫይረስ ወረረሽኝ ከቻይናዋ ዉሃን ከተቀሰቀሰ በኋላ ወደ አውሮፓ እና አሜሪካ በመሻገር በርካቶችን አጥቅቷል፤ ህይወትም ነጥቋል።
ወረርሸኙ ወደ ተለያዩ የአፍሪካ አገራት መዛመት ሲጀምር 'አፍሪካውያን ሊያልቁ ነው' የሚሉ መላምቶች ተሰምተዋል። በሚያዝያ ወር ላይ ሜሊንዳ ጌትስ ከሲኤንኤን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ የአፍሪካውያን አስከሬኖች በጎዳናዎች ላይ እንደሚረፈረፉም ታይቷቸው ነበር።
በአህጉሪቷ ውስጥ እስካሁን ባለው መረጃ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 125 ሺህ 640 ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 51 ሺህ 462ቱ አገግመዋል፤ 3 ሺህ 709 ሰዎችም ህይወታቸውን አጥተዋል።
ከአንድ ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ላላት አህጉር ቁጥሩ በቫይረሱ የተያዙት ሰዎች ቁጥር ትንሽ ነው የተባለ ሲሆን የዓለም ጤና ድርጅትም ሆነ ሌሎች የአህጉሪቷን ሁኔታ የሚተነብዩ ባለሙያዎች በአፍሪካ እንደተፈራው ላይሆን ይችላል እያሉ ነው።
ተጨማሪ ለማንበብ፡ በአፍሪካ ስላለው የኮሮናቫይረስ ዘገምተኛ አካሄድ ምን ማለት ይቻላል?
















