''አሜሪካ፤ ማስፈራራትሽን አቁሚ'' ቻይና
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እንደአዲስ ቻይና ላይ ትችት መሰንዘራቸውን ተከትሎ ቻይና የኮሮናቫይረስን ለመዋጋት መተባበር ብቻ ነው የሚያዋጣን ብላለች።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት "መንግሥታት ቫይረሱን በህብረት መዋጋት አለባቸው" ካለ በኋላ ነገር ግን ይህ ውጤታማ እንዲሆን አሜሪካ አብራን ልትሰራ ይገባል ብሏል። ''አሜሪካ፤ ማስፈራራትሽን አቁሚ'' ሲልም መሥሪያ ቤቱ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ሐሙስ ዕለት ፕሬዝደንት ትራምፕ ከቻይና ጋር ያላቸውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ እንደሚያቋርጡ ዝተው ነበር። ምክንያታቸው ደግሞ የቤጂንግ መንግስት የቫይረሱን ስርጭት እየወሰደ ያለው እርምጃ በቂ አይደለም ነው።
አሜሪካ በቻይናዋ ዢንጂያንግ ሰብአዊ ጥሰት እየተፈጸመ በመሆኑ አገሪቱ በሰብአዊ መብት ጥሰት መጠየቅ አለባት ካለች በኋላ ነው የሁለቱ አገራት ግንኙነት እየሻከረ የመጣው።