የናይሮቢ ከተማ ገዢ ለድሆች መጠጥ አቀርባለሁ አሉ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የዕለት ጉርሳቸውን ለመሸፈን ላልቻሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ከሚያቀርበው የምግብ እርዳታ ጋር አብሮ መጠጥ ሊያቀርብ እንደሆነ የከተማዋ ገዢ መናገራቸው መነጋገሪያ አድርጓቸዋል።
አገረ ገዢው ማይክ ሶንኮ ይህንን የተናገሩት ማክሰኞ ዕለት በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነበር።
ሶንኮ "አነስተኛ ጠርሙስ ሄነሲ [የኮኛክ መጠጥ ዓይነት ነው] በምግብ እድላው ላይ ጨምረን ለሕዝባችን እናቀርባለን" ማለታቸው ተሰምቷል።
የከተማዋ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በዚህ የአገረ ገዢው ንግግር ሲሳለቁ ተስተውሏል።
አገረ ገዢው አክለውም "በዓለም ጤና ድርጅትም ሆነ በሌሎች የጤና ተቋማት የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት አልኮል ኮሮናቫይረስንም ሆነ ሌሎች ቫይረሱችን ይገላል" ብለዋል።
በአገሪቱ በሚሰራጨው ሲትዝን ቲቪ የአገረ ገዢው አስተያየት ተደምጧል።
የመዲናዋ ናይሮቢ ገዢ በተናገሩት ነገር ደግሞ በርካታ ኬንያዊያን በማኅበራዊ መገናኛ መድረኮች ላይ እየተሳለቁበት ነው።
ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።
የ X ይዘት መጨረሻ

















