የዩናይትድ ኪንግደም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጀምስ ክሌቨርሊይ ሰላማዊ ሰዎች ለስቃይ ለመዳረጋቸው ተጠያቂው ሐማስ ነው አሉ።
ሚኒስትሩ ይህ ያሉት
ዛሬ ጠዋት ዩኬ የእስራኤል መንግሥት ጥቃቱን እንዲቀጥል ደግፋ እንደሆነ በተጠየቁበት ወቅት ነው።
ሚኒስትሩም ሲመልሱ “ለፍልስጥኤማውያን ስቃይ ተጠያቂው ሐማስ ነው” ብለዋል።
ሆኖም በተለይ እስራኤል የምድር
ጥቃት ከመጀመሯ ቀደም ብሎ በጋዛ እየደረሰ ያለው ሞት እንዳሳሰባቸው ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
እስራኤል በጋዛ ላይ እየወሰደችው
ባለው የቦምብ ዘመቻ ከ2 ሺህ 300 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የፍልጥኤም ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
ክሌቨርሊይ “ እስራኤል በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት የመቀነስ ግዴታ አለባት።በዚህ ጉዳይ ላይም ከእስራኤል መንግሥት ጋር በነበረኝ ውይይት ይህንኑ አንስቻለሁ” ብለዋል።
የኖርዌይ የስደተኞች ምክር
ቤት ዋና ጸሐፊ ሰላማዊ ሰዎች ከሰሜናዊ ጋዛ ወደ ደቡብ እንዲሄዱ መገደዳቸው እንደ ጦር ወንጀል ይቆጠራል ማለታቸውን ተከትሎም ዩኬ በእስራኤል ላይ የጦር ወንጀል ክስ አንስታ እንደሆነም ሚኒስትሩ ተጠይቀው
ነበር።
“የዩኬ መንግሥት ለዓለም
አቀፍ ሕግ መከበር ቁርጠኛ አቋም ነው ያለው” ሲሉ የእንግሊዝ መንግሥት እስራኤል የምትፈፅመውን ጥሰትም ዝም ብሎ እንደማያልፍ
ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ በመጨረሻም
የዩኬ መንግሥት በግብፅ እና በጋዛ ሰርጥ መካከል ያለውን የራፋህ መሻገሪያን ለመክፈት ከግብፅ እና ከእስራኤል ጋር እየተነጋገረ
መሆኑን፤ ነገር ግን እስካሁን አለመሳካቱን ተናግረዋል።