የዩክሬን ባለሥልጣን ሩሲያ በኪዬቭ ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሟን ገለጹ
የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደማይሮ ኩሌባ ሩሲያ በዩክሬን መዲና ኪዬቭ ላይ ‘አስከፊ’ የሚሳኤል ጥቃት መፈጸሟን አስታወቁ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ናዚ ጀርመን በዩክሬን ላይ ካደረገው ጥቃት ጋር አነጻጽረውታል።
በኪዬቭ ያለው የቢቢሲ ዘጋቢ ፖል አደምስ የአደጋ ማስጠንቀቂያ ደወል እና ቢያንስ አንድ የፍንዳታ ድምጽ በከተማዋ መስማቱን ተናግሯል።
አንድ የዩክሬን ጋዜጣ የሩሲያ ታንኮች ወደ መዲናዋ እንዳይገቡ የዩክሬን ወታደሮች በኪዬቭ አቅራቢያ የሚገኝ ድልድይ ማፍረሳቸውን ዘግቧል።