የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱን የትኛው ፓርቲ በበላይነት ይይዛል?

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ዋይት ሐውስ እና የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት ከዲሞክራቶች እጅ ወጥተዋል። ዶናልድ ትራምፕ ፕሬዝደንት ሲሆኑ ሴኔቱ ደግሞ በሪፐብሊካኖች የበላይነት ተይዟል።
ነገር ግን የተወካዮች ምክር ቤት የበላይነቱን የትኛው ፓርቲ ይይዛል የሚለው እስካሁን አልተወሰነም።
አሁን ባለው ሁኔታ የተመራጩ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ፓርቲ 211 መቀመጫዎችን እንደሚያሸንፍ ተገምቷል። ነገር የምክር ቤቱን የበላይነት ለማግኘት 218 መቀመጫዎቸን ማግኘት አለበት። በተቃራኒው ዲሞክራቶች እስካሁን ያገኙት መቀመጫ 199 ነው።
25 መቀመጫዎች እስካሁን አሸናፊያቸው ያልታወቀ ሲሆን ውጤታቸው በቅርቡ ይገለፃል ተብሎ ይጠበቃል።
ሪፐብሊካኖች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱን የበላይነት ካገኙ ሶስቱንም የመንግሥት መዋቅሮች ተቆጣጠሩ ማለት ነው። ይህ ከሆነ ዶናልድ ትራምፕ ያሻቸውን አጀንዳ ከማራመድ የሚያግዳቸው አይኖርም።
ዲሞክራቶች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱን ከተቆጣጠሩት ምናልባት ለትራምፕ የሥልጣን ዘመን የተመቹ እንደማይሆን ይጠበቃል።
ነገር ግን የቢቢሲ የአሜሪካ አጋር የሆነው ሲቢኤስ እንደሚገምተው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱን የበላይነት ሪፐብሊካኖች ሊወስዱት ይችላሉ።



















