ትራምፕ ይህንን ጦርነት የማስቆም አቅም አላቸው - የቀድሞ የእስራኤል ዲፕሎማት

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
እስራኤል እና በኢራን መካከል ያለውን ግጭት የማስቆም አቅም በአብዛኛው በዶናልድ ትራምፕ እጅ ነው ሲሉ ለሁለት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትሮች አማካሪ የነበሩት የቀድሞ ዲፕሎማት አሎን ፒንካስ ተናገሩ።
ፒንካስ ትራምፕ ሁለቱን አገራት ለማደራደር በሚያስችል ሁኔታ ላይ ናቸው ሲሉ ለቢቢሲ ኒውስዴይ ፕሮግራም ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኢራንን ለመታደግ እና በድርድር ላይ የተመሠረተ ሰላምን ለመቀበል የሚያስችላቸውን ሀሳብ ለቴህራን ሊያቀርቡ ይችላሉ።
ነገር ግን ኢራን ያለችበት ሁኔታ ለመደራደር ደካማ የሚባል ስለሆነ ትግሏን ለመቀጠል እና በእስራኤል ላይ የበለጠ ጉዳት ማድረስ ትፈልግ ይሆናል ብለዋል።
"በአንጻሩ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስልክ አንስተው ኔታንያሁ 'ይበቃል፤ ይህንን ለማቆም 24 ሰዓት አለህ' ሊሏቸው ይችላሉ።
"ከሁለቱ አንዱን ያደርጉ ይሆን? አላውቅም" ብለዋል የቀድሞው ዲፕሎማት።






















