በኢትዮጵያ ለቀድሞ ተዋጊዎች ተሃድሶ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ወጣ

የፎቶው ባለመብት, National Rehabilitation Commission
በኢትዮጵያ ከ80 ሺህ በላይ የሚሆኑ የቀድሞ ታጣቂዎችን ትጥቅ አስፈትቶ በማሰናበት ከሕብረተሰቡ ጋር በመቀላቀል ሂደት ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መደረጉን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ።
የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን እንደተናገሩት በተለያዩ ክልሎች ከ80 ሺህ በላይ የሚሆኑ የቀድሞ ተዋጊዎች በተሃድሶ ሂደት ውስጥ አልፈው ወደ ሰላማዊ ሕይወት መመለሳቸውን ተናግረዋል።
ከእነዚህ መካከል ከ63 ሺህ በላይ የሚሆኑ ከትግራይ ክልል መሆናቸውን ጠቅሰው ለዚህም ከ6.7 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አመልክተዋል።
የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ብ/ጄነራል ደርቤ መኩሪያ በበኩላቸው በእስካሁን የተሃድሶ ትግበራ ሂደት ከመከላከያ ሠራዊቱ ወጥተው “በሌላ ጎራ ከተሰለፉ ከ5200 በላይ የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ውስጥ 520 የሚሆኑት” በተሃድሶ ሂደት ውስጥ ማለፋቸውን ተናግረዋል።
















