በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ 302 ሺህ 728 የኮሮናቫይረስ ምርመራዎች ተደርገዋል
ባለፉት 24 ሰዓታት 5 ሺህ186 ናሙናዎች የኮቪድ-19 ምርመራ እንደተደረገላቸው ተገለፀ። ከእነዚህም መካከል 294 ሰዎች ላይ ኮሮናቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴርና የህብረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ አመልክተዋል።
በአዲስ አበባ 209፣ ኦሮሚያ 13፣ ትግራይ 31፣ ጋምቤላ 20፣ አማራ 9፣ አፋር 6፣ ድሬዳዋ፣ 4፣ ሶማሊ 2፣ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎችን አስመዝግበዋል።
በአሁኑ ሰዓት በጽኑ ሕሙማን የሚገኙ ሰዎች ቁጥር 36 ሲሆን ከሕመሙ ሙሉ በሙሉ ያገገሙ ደግሞ 51 መሆናቸው በመግለጫው ላይ ተመልክቷል።
ባለፉት 24 ሰዓታት ሁለት ሰዎች ሲሞቱ አንዱ ግለሰብ በአፋር ህክምና ክትትል እየተደረገለት የነበረ መሆኑ ሲነገር ቀሪው ግለሰብ ደግሞ በአዲስ አበባ ከአስክሬን ላይ በተወሰደ ናሙና መገኘቱ ተገልጿል።
በኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ 4768 ሰዎች ከኮቪድ-19 ሲያገግሙ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 148 ደርሷል።
በመላው ኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ከ300 ሺህ በላይ የኮሮናቫይረስ ምርመራዎች የተደረጉ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 8 ሺህ 475 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ታውቋል።