በኬንያ ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው በርካታ ታዳጊዎች አርግዘዋል

የፎቶው ባለመብት, AFP
የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመግታት ሲባል ከመጋቢት ወዲህ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ በርካታ ታዳጊዎች ማርገዛቸውን የኬንያ ባለሥልጣኖች ተናገሩ።
የጤና ሚንስቴር ያወጣው መረጃ እንደሚያሳየው፤ ዘንድሮ በአንድ ግዛት ብቻ ወደ 4 ሺህ ታዳጊዎች አርግዘዋል። አብዛኞቹ ታዳጊዎች ዘመዶች ለዚህ ተጠያቂ መሆናቸው እንዳሳሰባቸውም ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።
ያረገዙ ታዳጊዎች ትክክለኛ ቁጥር ሪፖርት ስለማይደረግ፤ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ከፍተኛ ሊሆን ይችላል።
በ47ቱም የኬንያ ግዛቶች ያሉ የፖለቲካ ኃላፊዎች መንግሥት ጉዳዩን እንዲመረምር ጠይቀዋል።
ኬንያ በታዳጊዎች እርግዝና በዓለም ከሚጠቀሱ አገሮች አንዷ ናት። ከ1,000 ነፍሰ ጡር ሴቶች 82 ያህሉ ታዳጊዎች ናቸው።







