በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ኮሮናቫይረስ ዳግም እየተሰራጨ ነው

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ትናንት የወጡ አሃዞች እንዳመላከቱት በበርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ ኮሮናቫይረስ ዳግም እየተሰራጨ ነው።
በደቡብ እና ምዕራብ አሜሪካ በሚገኙ ግዛቶች ደግሞ ስርጭቱ አይሎ ታይቷል። ከጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ የተገኘው አሃዝ እንደሚያመላክተው በ16 ግዛቶች በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።
አሪዞና፣ አላባማ፣ ዋሽንግተን፣ ሳውዝ ካሮላይና፣ ዩታህ፣ ቴክሳስ፣ ሚሲሲፒ፣ ፍሎሪዳ እና ጆርጂያ ቫይረሱ እየተሰራጨባቸው ይገኛል ከተባሉት ግዛቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።
በአሪዞና የሚገኙ ሆስፒታሎች እስከ አቅማቸው ጫፍ ድረስ ታማሚዎች እየተቀበሉ ነው።
እስካሁን ድረስ በአሜሪካ 119ሺህ ገደማ ሰዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ህይወታቸውን አጥተዋል።


















