ላስ ቬጋስ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ ጀመረች
በላስ ቬጋስ ስፖርታዊ ውድድሮች መመለስ ጀምረዋል። የብራዚሉ ጊልበርት በርንስ የቀድሞው የአሜሪካ ‘ዌልተርዌይት’ ሻምፒዮኑ ታይሮን ዉድሊን ባሸነፈበት የዩኤፍሲ ግጥሚያ ደግሞ የመጀመሪያው ሆኗል።
በፍሎሪዳ በቀጥታ በተላለፈው ጨዋታ ምንም አይነት ተመልካች በግጥሚያው ቦታ ያልነበረ ሲሆን አካላዊ ርቀትን በጠበቀ ሁኔታ ውድድሩ መስተናገዱ ተገልጿል።
የነቫዳ ግዛት አትሌቲክ ኮሚሽን ባሳለፍነው ሳምንት ነበር የፍልሚያ ውድድሮች በላስ ቬጋስ መካሄድ እንዲጀምሩ የፈቀደው።
የቦክስ ውድድር አዘጋጁ ቶፕ ራንክ ደግሞ ሰኔ ሁለት በሻኩር ስቲቨንሰን እና ፌሊክስ ካራባሎ መካከል የሚካሄድ ሌላ ፍልሚያን ሲያስተዋውቅ ነበር።