በኢትዮጵያ የአንድ ወር ጨቅላ ላይ የኮሮናቫይረስ ተገኘ

በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ መያዛቸው በምርመራ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 1257 ደርሷል። እስካሁን ድረስ በኮቪድ-19 ከተያዙት መካከልም 12 ሰዎች መሞታቸውንም የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። የወረርሽኙ ስርጭት በስፋት የሚታየው አዲስ አበባ ሲሆን በሌሎች ክልሎችም በአነስተኛ ቁጥር ይሁን እንጂ ተከስቷል። እስካሁን ድረስ በአገሪቱ በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 209 ሰዎች ማገገም ችለዋል። ማንኛውም ሰው ራሱንም ሆነ ሌሎችን ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መታደግ የሚችለው አካላዊ ርቀቱን ሲጠብቅ፣ እጁን በተደጋጋሚ በሳሙናና በውሃ ሲታጠብ እንዲሁም አፉንና አፍንጫውን ሲሸፍን መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይመክራሉ።

የቀጥታ ሽፋን

  1. የአርሜንያው ጠቅላይ ሚኒስትርና ቤተሰባቸው በኮቪድ-19 ተያዙ

    የአርሜንያ ጠቅላይ ሚንስትር ኒኮል ፓሺኒያን በኮሮናቫይረስ መያዛቸውን ገለፁ።

    "ምንም ዓይነት ምልክት አይታይብኝም፤ የኮሮናቫይረስ መከላከል ላይ የተሰማሩትን ለመጎብኘት ሳቅድ ነበር ልመረመር የወሰንኩት" ብለዋል በፌስቡክ የቀጥታ መልዕክታቸው ወቅት።

    አክለውም ቤተሰባቸውም በአጠቃለይ በቫይረሱ መያዛቸውን አስታውቀዋል።

    ባለፈው ሳምንት ከፍተኛ ነው የተባለ የሰው ቁጥር በኮቪድ-19 መያዙ ቢታወቅም አርሜንያ አሁንም የእንቅስቃሴ ገደብ ለማስቀመጥ አልወሰነችም።

    ከዚህ ይልቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማህበራዊ ርቀትን መጠበቅ እንዲሁም የእጅን ንጽህና በተደጋጋሚ መጠበቅን መክረዋል።

    በአርሜንያ ከ9000 በላይ ሰዎች በኮሮና መያዛቸው በምርመራ ሲረጋገጥ ከእነዚህም መካከል 131 ሰዎች ሞተዋል።

  2. "ጆርጅ ፍሎይድን አንቆ የገደለው ፖሊስ 'አስቦና አቅዶ' ነው"

  3. የቦልሶናሮ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ብራዚልን በተቃውሞ እየናጥዋት ነው

    የሳዎ ፓውሎ እና ሪዮ ዲ ጄኔሮ መንገዶች በቦልሶናሮ ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች ግጭት ሞቀዋል።

    ኮቪድ-19 ያልገታቸው ብራዚላውያን የአነጋጋሪው ፕሬዝደንት ጃይር ቦልሶናሮ ደጋፊና ተቃዋሚ በመሆን መንገዱን ቢቆጣጠሩም ፖሊስ መሃል ገብቷል።

    ቅዳሜና እሁድ በተደረጉ ምርመራዎች በብራዚል በቫይረሱ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 29 ሺህ ደርሷል።

    ቦልሶናሮ በፈረስ ተጭነው ደጋፊዎቻቸውን ተቀላቅለዋል። ኮቪድ-19ን በማጣጣል የሚታወቁት ቦልሶናሮ የአካላዊ ርቀት ጉዳይ ጉዳይ ያሳሰባቸው አይመስልም።

    የፕሬዝደንቱ ደጋፊዎች የሃገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይዘጋ ባይ ናቸው። ቦልሶናሮና የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ውጥረት ላይ ናቸው። ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝደንቱ ላይ ምርመራ ይደረግ ማለቱ ነው።

    ሳዎ ፓውሎ ውስጥ ፖሊስ ሰልፈኞችን ለመበተን አስለቃሽ ጭስ ተጠቅሟል።

    ምንም እንኳ ብራዚላውያን ጎራ ለይተው ተቃውሞ ቢወጡም በሃገሪቱ በኮሮናቫይረሱ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከቀን ቀን በሺዎች እየጨረ ነው።

  4. የፕሬዝዳንት ትራምፕን ገመና ያጋለጠው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ

  5. ከእንቅስቃሴ ገደብ መነሳት በኋላ ዓለም ምን ትመስል ይሆን?

  6. ሁለቱ አሜሪካውያን በግል መንኩራኩር ሕዋ በመርገጥ ታሪክ ሰሩ

  7. በኬንያ 31 እስረኞች በኮሮናቫይረስ ተያዙ

    በኬንያ ዋና መዲና ናይሮቢ 31 እስረኞች በኮሮናቫይረስ ተይዘው በመገኘታቸው ሆስፒታል ገቡ።

    እነዚህ እስረኞች ከሌሎች 28 እስረኞች ጋር የነበሩ ሲሆን ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ ለ21 ቀን በለይቶ ማቆያ ተቀምጠው ነበር ተብሏል።

    የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር ጄነራል የሆኑት ዋይክሊፍ "በመላ አገሪቱ በሚገኙ 129 እስር ቤቶች ውስጥ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እንዳይሰራጭ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሌ አድርገናል" ብለው ነበር።

    በኬንያ እስር ቤቶች የተጨናነቁ ናቸው።

    መንግሥት በቅርቡ የኮሮናቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በሚል በቀላል ጥፋት በእስር ላይ የነበሩ 11,000 ታራሚዎችን መልቀቁ ይታወሳል።

  8. ደቡብ አፍሪካውያን ወደ ትምህርት ቤት ሊመለሱ ነው

    ደቡብ አፍሪካ በዚህ ሳምንት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሳሉ ብላ አቅዳ ነበር። ነገር ግን ትምህርት ቤቶች በሚገባ እንዲዘጋጁ ለማስቻል በሚል በአንድ ሳምንት መገፋቱ ተገልጿል።

    የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ሲሆን መምህራኖች ግን ከዛሬ ጀምሮ በትምህርት ቤታቸው በመገኘት የኮሮናቫይረስን በትምህርት ቤቶች እንዳይስፋፋ እንዴት መከላከል እንደሚቻል ስልጠና ይወስዳሉ።

    ደቡብ አፍሪካውያን ከዛሬ ጀምሮ የአልኮል መጠጥ መግዛት የተፈቀደላቸው ሲሆንቤተ እምነቶች፣ መስጂዶች እስከ 50 ሰው ድረስ ብቻ ለማስተናገድ ተፈቅዶላቸዋል።

    የመሰረታዊ ትምህረት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶች መክፈቻ ጊዜ የዘገየው የሚመለከታቸው አካላት ከመከሩበት በኋላ መሆኑን አስታውቋል።

    ደቡብ አፍሪካ 32, 683 ሰዎች ኮሮናቫእረስ መያዛቸውን በምርመራ ስታረጋግጥ ከእነዚህም መካከል including 683 ሰዎች ሞተዋል።

  9. የ100 ዓመቷ አዛውንት ከኮቪድ-19 አገገሙ

    ኢንዶኔዢያ ውስጥ የ100 ዓመቷ ባልቴት ከኮሮናቫይረስ ድነዋል።

    የሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት አዛውንቷ ከኮቪድ-19 የዳኑ በዕድሜ ትልቋ ሴት ናቸው።

    ካምቲም የተሰኙት አዛውንት ከቫይረሱ ማገገማቸው ከታወቀ በኋላ በሃገሪቱ ሁለተኛዋ ትልቅ ከተማ ሱራባያ ከሚገኘው ሆስፒታል እንዲወጡ ተደርገዋል።

    የአዛውንቷ ዘመድ የሆነች ግለሰብ ኤኤፍፒ ለተሰኘው የዜና ወኪል እንደተናገረችው የ100 ዓመቷ አዛውንት ሊድኑ የቻሉት ራሳቸውን በዲስፕሊን በመንከባከባቸው ነው።

    ሁሌም ነርሶችን ስጠይቅ መድኃኒቷን በአግባቡ እንደምትወስድና ራሷን እንደምትንከባከብ ይነግሩኛል ትላለች የአዛውንቷ ዘመድ። ኢንዶኔዥያ 26 ሺህ ሰዎች በኮሮናቫይረስ እንደተያዙባት ይፋ አድርጋለች። የሟቾች ቁጥር ደግሞ 1613 ነው።

  10. የደቡብ ኮሪያ ቤተ እምነቶችና ኮሮናቫይረስ

    ደቡብ ኮሪያ እሁድ እለት በጊዮንጊ አውራጃ በሚገኝ ቤተ እምነት ውስጥ ኮሮናቫይረስ የተያዙ 30 ሰዎች ማግኘቷን አስታወቀች።

    አገሪቱ በሴኡል አቅራቢያ ቡሼዩን በሚገኝ አንድ ድርጅት ኮቪድ-19 የተያዙ 112 ሰዎችን ማግኘቷን አስታውቃ ነበር።

    ደቡብ ኮሪያ ከቤተ እምነቶች ጋር በተያያዘ ወረርሽኙ ዳግም ይስፋፋል የሚል ስጋት አላት።

    በየካቲት ወር ከፍተኛ ቁጥር የለው ሰው በኮሮናቫይረስ ተይዞ ያገኘችው ከ ሺንቺዮንጂ ቤተ ክርስትያን ጋር በተያያዘ ነበር። ከዚያም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቤተ እምነቱ የዳኤጉ ቅርንጫፉ ተይዘው ተገኙ።

    ከዚያ በኋላም አገሪቱ ቤተ እምነቶችን የዘጋች ሲሆን ቫይረሱን ከተቆጣጠረችው በኋላ ባለፈው ወር ዳግም ቤተ እምነቶቹ ተከፍተዋል።

  11. ደቡብ አፍሪካዊያን መጠጥ መግዛት ናፍቋቸዋል

  12. በብራዚል በአንድ ቀን ብቻ 33 ሺህ ሰዎች በኮሮና ተያዙ

  13. አሜሪካ ለብራዚል 2 ሚሊዮን የወባ መድኃኒት ልካለች

    ዩናይትድ ስቴትስ ሁለት ሚሊዮን ሃይድሮክሲክሎሮኪን ክኒናዎች ለብራዚል ልካለች።

    ምንም እንኳ ለወባ በሽታ እንደ መድኃኒትነት የሚያገለግለው ሃይድሮክሲክሎሮኪን ለኮሮናቫይረስ በሽተኞች መሰጠት የለበትም ቢባልም አሜሪካ ግን ወደ ብራዚል እያጋዘችው ነው።

    የዓለም የጤና ድርጅት መድኃኒቱን በኮቪድ-19 በሽተኞች ላይ እየሞከረ ነበር። ነገር ግን ከቀናት በፊት ሙከራው እንዲቋረጥ አዟል።

    የብራዚልና አሜሪካ መሪዎች ግን መድኃኒቱ ለኮቪድ-19 ወሳኝ ነው ሲሉ ይከራከራሉ።

    ፕሬዝደንት ትራምፕ እንደውም ለማንኛውም ብዬ አንድ ሁለት ክኒና እቅማለሁ ማለታቸው አይዘነጋም፤ የብራዚሉ አቻቸው ጃይር ቦልሶናሮም የ93 ዕድሜ ያላቸው እናቴ ካስፈለጋቸው በሚል በትንሽዬ ሳጥን አዘጋጅቼ አስቀምጫለሁ ይላሉ።

    የወባ በሽታ መድኃኒቶች ለኮቪድ-19 እንደሚያገለግሉ እስካሁን አልተረጋገጠም። የዓለም ጤና ድርጅት መድኃኒቶቹ ለሌላ በሽታ ሊያጋልጡ ይችላሉ ሲል ይመክራል።

  14. እንዴት አደራችሁ?

    የቢቢሲ አማርኛ ወዳጆች እንዴት አደራችሁ? ዕለተ ሰኞ በያላችሁበት ያማረ እንደሆነ እናምናለን። ዓለምን እያሸበረ ያለው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን የተመለከቱ ዘገባዎች በትኩስ በትኩሱ የምናደርስበት የቀጥታ ዘገባ ገፃችን እነሆ ጀምሯል። በድረ-ገፃችንና በፌስቡክ ገፃችን ለናንተ ይመጥናሉ ያልናቸውን መረጃዎች ማሠራጨት እንጀምራለን።

    በያላችሁበት ጥንቅቄ እንዳይላችሁ ማሳሰብ እንወዳለን።

    መልካም ቀን!

  15. በአፍሪካ ስላለው የኮሮናቫይረስ ዘገምተኛ አካሄድ ምን ማለት ይቻላል?

  16. በኢትዮጵያ ተጨማሪ 109 በቫይረሱ ሲያዙ፤ የሦስት ሰዎች ህይወት አለፈ

    ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 2836 የላብራቶሪ ምርመራ 109 ሰዎች ኮሮናቫይረስ ተጘኝቶባቸዋል።

    ከዚህም በተጨማሪ ከኮሮናቫይረስ ጋር በተያያዘ የሶስት ሰዎች ሕይወት ማለፉንም የጤና ሚኒስቴርና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዪት በጋራ የሚያወጡት ዕለታዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

    ሟቾቹም፣ አንደኛዋ የ29 አመት በትግራይ ክልል የሰቲት ሁመራ ነዋሪ ፣ ሁለተኛ የ75 አመት እድሜ ሴት የአዲስ አበባ ነዋሪና ሶስተኛዋ ደግሞ የ55 አመት በደቡብ ክልል የከፋ ዞን ነዋሪ በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ የመጡ መሆናቸው ተገልጿል። ሃገሪቷም በኮሮናቫይረስ ያጣቻቸው ሰዎች ቁጥር 11 ደርሷል።

    ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው የእድሜ ክልል ከ 5 እስከ 70 ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል የቫይረሱ ስርጭት ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ 99 ሰዎች ተገኝተዋል።

    ቀሪዎቹ ሁለት ሰዎች ከትግራይ፣ አምስት ከኦሮሚያና ሶስቱ ደግሞ ከሐረሪ መሆናቸውንም መግለጫው ጠቁሟል።

    በዚህም መሰረት በአጠቃላይ በሃገሪቱ በበሽታው የተያዙትን ቁጥር ወደ 1 ሺህ 172 የደረሰ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል 209 አገግመዋል።

  17. ከጀርመን ወደ ቻይና በተደረገ በረራ ላይ በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ

    በትናንትናው ዕለት ከጀርመን ወደ ቻይና በተደረገ የቻርተር በረራ ላይ አንደኛው ግለሰብ በኮሮናቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል።

    ከፍራንክፈርት መነሻውን ያደረገው ይህ በረራ ቻይና ውስጥ ሰራተኛ የሆኑ 200 የሚጠጉ ጀርመናውያን መንገደኞች ከነቤተሰባቸው የተሳፈሩበት ነው ተብሏል።

    የኮሮናቫይረስ መኖሩ የተረጋገጠበት ግለሰብ የ34 ዓመት መሐንዲስ ሲሆን ከፍተኛ ሙቀት ቢኖርበትም ምልክቶች አልታዩበትም ተብሏል።

    በአካባቢ ወደሚገኝ የጤና ማዕከልም ለህክምና ተወስዷል።

    ሁሉም መንገደኞች ለሁለት ሳምንት ያህል በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ የሚገቡ ሲሆን ከዚያ በኋላም ምርመራ ይደረግላቸዋል ተብሏል።

  18. ከደቡብ አፍሪካ ልምዶች አፍሪካ ምን መማር ትችላለች?

    ደቡብ አፍሪካ በአህጉቱ በብዙ ነገር ግንባር ቀደም ነች። ከኮሮናቫይረስ ወረርሽን ጋር በተያያዘም ጥሩም ሆነ አስጊ የሚባሉ ውሳኔዎችን ስታሳልፍ ብዙዎች እንደ ምሳሌ ተመልክተዋታል።

    ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፎሳ የኮሮናቫይረስ ወረረርሽኝን ለመቆጣጠር የወሰዱት እርምጃ በብዙዎች ቢያስመሰግናቸውም የሚተቿቸውም አልጠፉም።

    ከነገ ጀምሮ ደቡብ አፍሪካ ከሁለት ወራት በኋላ ኢኮኖሚዋን መክፈት የምትጀምር ሲሆን እህ ውሳኔ ለፕሬዝዳንቱ ከባድ ፈተና እንደሚሆንባቸው ይጠበቃል።

    ደቡብ አፍሪካ ወረርሽኙ ሳይከሰት በፊት ኢኮኖሚዋ መድቀቅ ጀምሮ ነበር።

  19. በሎስ አንጀለስ ባለው ተቃውሞ ምክንያት የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት ተዘጉ

    በሚኒያፖሊስ በነጭ ፖሊስ አንገቱን ተረግጦ ሕይወቱ ያለፈችው ጥቁር አሜሪካዊው ጆርጅ ፍሎይድን ሞት ተከትሎ ብዙዎች ለተቃውሞ ጎዳና ላይ ወጥተዋል።

    ይህንንም ተከትሎ በሎስ አንጀለስ የሚገኙ ባለስልጣናት የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላትን ዘግተዋል።

    የሎስ አንጀለስ ከንቲባ ኤሪክ ጋርሴቲ ለሪፖርተሮች እንደተናገሩት ማዕከላቱ የተዘጉት ለጥንቃቄ እንደሆነ አስረድተዋል። “ወደየቤታችሁ መሄድ ያለባችሁ ወቅት ነው። ሁኔታዎች ደህና ሲሆኑ ተመለሱ፤ በሰላም ተቃወሙ” ብለዋል።

    በአገሪቱ በተለያዩ ግዛቶች እየተጠናከረ ያለውንም ተቃውሞ ለመቆጣጠር በሚል የሰዓት እላፊ አዋጅ ተጥሏል።

    የሚኒሶታ አስተዳዳሪ ቲም ዋልዝ ተቃዋሚዎቹ የፊት ጭምብል እንዲያደርጉና አካላዊ ርቀታቸውንም እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፈዋል።

    የኒውዮርክ አስተዳዳሪ አንድሪው ኩሞ በበኩላቸው የጆርጅ ፍሎይድ መገደል እንዲሁም በኮሮናቫይረስ የሚሞቱት አብዛኛዎቹ ጥቁር አሜሪካውያን መሆናቸው፤ በአጠቃላይ በአሜሪካ ያለውን ስር የሰደደ መዋቅራዊ ዘረኝነት ያጋለጠ ነው ብለዋል።

    አክለውም ብዙዎች ቁጣቸውን እየገለጹ ያሉት በዚህ የተጠራቀመ ጭቆና ነው በማለት በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል።

  20. አርጀንቲናውያን የእንቅስቃሴ ገደቡን ተቃውመው ሰልፍ ወጡ

    በመቶዎች የሚቆጠሩ አርጀንቲናውያን አገሪቱ ያስቀመጠችውን ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብ በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።

    መንግስት ከሁለት ወራት በፊት ተግባራዊ ያደረገውን ገደብ ማብቂያ እንዲያበጅለትም ጠይቀዋል።

    በዋና ከተማዋ ቦነስ አይረስ እና ሌሎች ከተሞች ሰልፍ የወጡት ዜጎች ፕሬዝደንት አልቤርቶ ፈርናንዴዝ ልክ እንደ አምባገነን እያደረጋቸው ነው በማለት የንግድ ተቋማት ተመልሰው እንዲከፈቱ ጠይቀዋል።

    ሌሎች ሰልፈኞች ደግሞ ከኮሮናቫይረስ ጋር የተያያዙ እንደ 5ጂ ኔትዎርክና ክትባትን የተመለከቱ መልእክቶችን ይዘው ታይተዋል።

    አርጀንቲና ውስጥ 500 የሚደርሱ ሰዎች በኮሮረናቫይረስ ምከንያት ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን 16 ሺ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።