"ክትባት ካልተገኘ በስተቀር የኦሊምፒክ ውድድር ላይካሄድ ይችላል"

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
በኮሮናቫይረስ ወረርሽን ምክንያት ወደ ቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት የተሸጋገረው የኦሊምፒክ ውድድር የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ እንደሆነ ተነገረ።
በዓለማችን ካሉ ቀዳሚ የጤና ሳይንቲስቶች መካከል አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ዴቪ ስሪድሃራ እንደተናገሩት አስከ ውድድሩ መካሄጃ ጊዜ ድርስ የኮሮናቫይረስ ክትባት ካልተገኘ የቶኪዮው ኦሊምፒክ ሊካሄድ ይችላል ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።
በዓለም ዙሪያ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ከተቋረጡ ወራት ተቆጥረዋል። በተጨማሪም በመጪዎቹ ወራት ይካሄዳሉ ተብለው የታቀዱ ውድድሮችም ተሰርዘዋል።
የስፖርት ባላስልጣናት የዚህ ዓመት መረሃ ግብሮቻቸውን መቼ ማጠናቀቅ እንደሚችሉና ቀጣይ የሚደረጉ ውድድሮች መቼ ሊካሄዱ እንደሚችሉ ከወዲሁ እየመከሩ ነው።
















