ደቡብ ኮሪያ ለአሜሪካ የመመርመሪያ ኪቶች ልትልክ ነው
የደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንት ሙን ዤ-ኢን አሜሪካ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪቶች እንድትሰጣቸው መጠየቃቸውን ተናገሩ።
ይህንን ያሉት በዋና ከተማዋ ሴኡል የመመርመሪያ ኪት አቅራቢን በጎበኙበት ወቅት ነበር።
አክለውም ለዓለም የመመመርመሪያ ኪት ለመላክ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።
"ትናንት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፍጥነት የመመርመሪያ ኪት እና የለይቶ ማቆያ ምርቶችን አንድንልክላቸው ጠይቀውናል" ብለዋል ፕሬዝዳንት ሙን።
የፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት አክሎም ደቡብ ኮሪያ ትርፍ ቁሳቁስ ካለ ለመላክ ፈቃደኛ መሆኗን አስታውቋል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters









