የተኩስ አቁም እስኪደረሰ ታጋቾች እንደማይለቀቁ የሐማስ ተወካይ ተናገሩ
ሞስኮን በመጎብኘት ላይ የሚገኙ የሐማስ የልዑካን ቡድን አባል ከእስራኤል የተወሰዱ ታጋቾች የተኩስ አቁም ስምምነት እስኪደረስ ድረስ እንደማይለቀቁ መናገራቸውን አንድ የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ዘገበ።
የሩሲያው ኮመርሳንት ጋዜጣ አቡ ሐሚድን ጠቅሶ እንደዘገበው ሐማስ ታጋቾችን በሙሉ ለማግኘት ጊዜ ይፈልጋል ብለዋል።
"አብዛኛዎቹ ሲቪሎች የሆኑ በርካታ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ውለዋል። በጋዛ ሰርጥ ውስጥ ፈልገን እስከምናገኛቸው ጊዜ እንፈልጋለን" ሲሉ ሐሚድ ተናግረዋል።
እስካሁን አራት ታጋቾች "በሰብአዊ ምክንያቶች" በሐማስ ተለቀዋል። እናት እና ሴት ልጃቸው ጁዲት እና ናታሊ ራናን ጥቅምት 20 ሲለቀቁ፤ የ85 ዓመቷ ዮቼቭድ ሊፍሺትዝ እና የ79 ዓመቷ ኑሪት ኩፐር ሰኞ ተለቀዋል።