ሩሲያ ተገደው የገቡ የሠራዊት አባላትን አሰማርታለችተባለ
ዩናይትድ ኪንግደም የሞስኮ አስተዳደር በዩክሬን ጦርነት ሠራዊቱን ተገደው የተቀላቀሉ ወታደሮችን አሰማርቷል አለች።
ይህ የተባለው የዩኬ መንግሥት ስለ ጦርነቱ በወቅታዊው የወታደራዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ በሚያወጣውመግለጫ ነው።
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዚህ ሳምንት ጭምር ሰዎች ተገገው በጦርነቱ ተሳታፊ እንደማይሆኑ ቢገልጹም ሞስኮ ግን ሰዎች ያለ ፍላጎታቸው እንዲዋጉ እያደረገች ነው ስትል ዩናይትድ ኪንግደም አስታውቃለች።
ዩናይትድ ኪንግደም ባወጣችው አጭር መግለጫ “ጉዳቶቹ እየጨመሩ ስለሄዱ ፕሬዝዳንት ፑቲን ተተኪዎችን ፍለጋ ከሩሲያ ጦር ኃይሎች እና ከሌሎች ምንጮች ለማዝመት ይገደዳሉ” ብላለች።
በተጨማሪም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የሩሲያ አየር ጥቃት “በከፍተኛ ደረጃ” መቀነሱን ተገልጿል።
በሰሜን ምዕራብ ኪዬቭ የሚገኘው የሩሲያ ጦር መግፋት የቻለው በአነስተኛ መጠን ከመሆኑ ባለፈ “በዩክሬን ጦር ኪሳራ እየደረሰበት ነው” ተብሏል።
እንደ አንድ ሪፖርት ግምት ከሆነ እስካሁን ወደ 5,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ተገድለዋል።