በሕንድ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ግማሽ ሚሊየን ደረሰ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ሕንድ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ 100 ሺህ ሰዎች በኮሮናቫይረስ እንደተያዙባት ይፋ አድርጋለች። ይህ በአገሪቱ ጠቅላላ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ግማሽ ሚሊየን አድርሶታል።
የጤና ሚኒስቴር ሰዎች ወረርሽኙ በፍጥነት እየተስፋፋ ነው ይላሉ።
ትላንት [አርብ] ብቻ አገሪቱ በአንድ ቀን 18 ሺዎች ሰዎች በቫይረሱ እንደተያዙ ይፋ አድርጋለች። ይህም ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል።
በምዕራባዊ ሕንድ የምትገኘው የማሃራሽትራ ግዛት በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ እጅግ ከተጠቁ ግዛቶች ቁንጮዋ ናት።
አንዳንድ የጤና ሰዎች መንግሥት አሁን ትኩረቱን ወረርሽኙን ከመግታት ይልቅ ለሞት መጠን መቀነስ ቢያደርግ ይሻላል ይላሉ።
ሕንድ ባለፈው መጋቢት ጠበቅ ያለ የእንቅስቃሴ ገደብ ብትጥልም፤ ገደቦቹ በዚህ ወር መጀመሪያ አካባቢ መላላታቸውን ተከትሎ ወረርሽኙ ማገርሸት ጀምሯል።











