"ኮሮናቫይረስን አሜሪካ ለኢራን የሰራችው ነው" አያቶላህ አሊ ሃሚኒ
የኢራን ሐይማኖታዊ የበላይ መሪ አገራቸው የኮሮናቫይረስን ለመዋጋት ለምታደርገው ጥረት ከአሜሪካ የቀረበላትን እርዳታ የመስጠት ጥያቄ እንደማይቀበሉት አሳወቁ።
አያቶላህ አሊ ሃሚኒ በቴሌቪዥን ቀርበው ባደረጉት ንግግር ላይ እንዳሉት አሜሪካ የኢራን "ከሁሉ የባሰች ጠላት" ናት በማለት ቀደም ሲል አሜሪካ ለወረርሽኙ መከሰት ተጠያቂ ናት ሲሉ አንዳንድ የቻይና ባለስልጣናት ያቀረቡትን የሴራ ትንተና ክስ ጠቀስ አድርገዋል።
"ይህ ክስ ምን ያህል እውነተኛ መሆኑን አላውቅም ነገር ግን እየተነገረ ነው፤ ታዲያ አእምሮው በትክክል የሚሰራ ሰው መድሃኒት ይሰጡኛል ብሎ እምነት ይጥልባቸዋል?" ሲሉ የጠየቁት ሃሚኒ "ስለዚህም የምትሰጡን መድሃኒት ቫይረሱን የበለጠ ለማስፋፋት የምትጠቀበት መንገድ ነው" ሲሉ አሜሪካንን ከሰዋል።
መሪው ጨምረውም ምንም ማስረጃ ሳያቀርቡ "የኮሮናቫይረስ የኢራናዊያንን የዘረመል መረጃ በተለያዩ መንገዶች በመውሰድ በተለየ ሁኔታ ለኢራን የተሰራ ነው" ሲሉ ጣታቸውን አሜሪካ ላይ ቀስረዋል። ሙሉውን ለማንበብ ይህንን ይቻኑ ኢራን ከአሜሪካ ቀረበላትን የህክምና እርዳታ አልቀበልም አለች