ፕሬዝዳንት አል በሽር ከስልጣን ወረዱ

ላለፉት 30 ዓመታት ሱዳንን ያስተዳደሩት ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አል በሽር ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቁ ተቃውሞዎች መሰማት የጀመሩት ከወራት በፊት ነበር። አል በሽር ተቃውሞውን አለዝበው በመንበራቸው ላይ ለመቆየት የተለያዩ እርምጃዎችን ቢወስዱም የተቃዋሚዎቻቸው ፍላጎት ስላልረካ አመጹ ቀጥሎ ቆይቷል። በመጨረሻም በጦር ሠራዊታቸው ከስልጣናቸው ተነስተው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የቀጥታ ሽፋን

  1. ኢትዮጵያውያን በሱዳን በዚህ ሰዓት, "ስራ የለም ወደ ቤታችሁ ተመለሱ"

    ፕሬዝዳንት አልበሺር

    በካርቱም የሚኖረው ኢትዮጵያዊ መሀመድ ዚን ለቢቢሲ እንደተናገረው አሁን ያለሁበት ቦታ 'ሚናል ባሪ' የሚባል ሲሆን ትርጉሙም መናኸሪያ ማለት ነው።

    እንደተለመደው ጠዋት ለሥራ መውጣቱን የተናገረ ሲሆን "ሥራ ቦታ እንደደረስኩኝ ዛሬ ሥራ የለም ወደቤታችሁ ሂዱ ተባልን" ብሏል።

    ሱዳናውያን ለአምስተኛ ጊዜ ቀንና ለሊት የሚያደርጉትን ተቃውሞ የቀጠሉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም ወደ ፕሬዝዳንቱ ቢሮ አልቂሃዳ ተሰብስበው እየተመሙ ነው ሲል ነግሮናል።

    እየተወራ እንዳለው ይላል ዚን "ዛሬ ፕሬዝዳንቱ ስልጣናቸውን ይለቃሉ ተብሎ ይጠበቃል" ብሏል።

  2. ለወራት የዘለቀው ተቃውሞ, ለወራት የዘለቀው ተቃውሞ

    ተቃዋሚዎች

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

    የምስሉ መግለጫ, ተቃዋሚዎች

    ለሰላሳ ዓመታት ስልጣን ላይ የቆዩት አልበሽር ላይ ተቃውሞ የተቀሰቀሰው ከባለፈው ሕዳር ወር ጀምሮ ነበር።

    ተቃውሞዎቹ መጀመሪያ ላይ የተቀሰቀሱት የኑሮ ውድነትን ምክንያት አድርገው የነበረ ሲሆን በኋላ ላይ ተቃዋሚዎቹ አልበሽር ከስልጣን እንዲለቁ የሚጠይቁ ተቃውሞዎችን ለወራት አድርገዋል።

    የተቃዋሚዎቹ ተወካዮች ከሃገሪቱ ሠራዊት ጋር የሽግግር መንግሥት በሚቋቋምበት ሁኔታ ላይ ለመነጋገር ሲጠይቁ ቆይተዋል።

    ከተቃውሞው መሪዎች መካከል አንዱ የሆነው ኦምር ኤልዲጊር ባለፈው ሳምንት ለኤኤፍፒ እንደተናገረው ተቃዋሚዎቹ "የአብዮቱን ፍላጎት የሚወክል " መንገድ እንደሚፈልጉ ተናግሯል።

    የሃገሪቱ ፖሊስም መኮንኖቹ በተቃዋሚዎች ላይ እርምጃ እንዳይወስዱ ትዕዛዝ አስተላልፏል። ማክሰኞ ዕለት የፖሊስ ቃል አቀባይ "ሰላማዊ የስልጣን ሽግግርን ሊያመጣ የሚችል ስምምነት" እንዲደረስ ጥሪ አቅርበዋል።

    የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ቡድኖች መንግሥት ተቃዋሚዎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ወስዷል በማለት ሲወቅሱ ቆይተዋል።

    በታህሳስ ወር በተጀመረው ፀረ መንግሥት ተቃውሞ 38 ሰዎች መሞታቸውን የመንግሥት ባለስልጣናት የገለጹ ሲሆን የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪው ሂዩማን ራይትስ ዋች ግን ቁጥሩ ከተጠቀሰው በላይ መሆኑን ይናገራል።

    የሕዝባዊው ተቃውሞ ሳይቋረጥ በመቀጠሉ የካቲት ወር ላይ አል በሽር ስልጣናቸውን ይለቃሉ ተብሎ ቢጠበቅም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመላው ሃገሪቱ አውጀዋል።

  3. ሱዳናውያን የፕሬዝዳንታቸውን የመውረድ ዜና በጉጉት እየጠበቁ ነው, ሱዳናውያን የፕሬዝዳንታቸውን መውረድ ዜና በጉጉት እየጠበቁ ነው

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    ሱዳናውያን የጦር ኃይሉ ይሰጣል ተብሎ የሚጠበቀውን መግለጫ በጉጉት እየጠበቁ ነው።

    ከስልጣን መውረዳቸው አይቀርም የሚለው ግምት በሕዝቡ ዘንድ ቢኖርም እስካሁን ግን ይፋዊ መግለጫ አልተሰጠም።

    ሱዳን ነፃነቷን ካገኘችበት እ.ኤ.አ 1956 ጀምሮ ጦሩ በሀገሪቱ ፖለቲካው ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ አለው።

    ሱዳናዊ ጋዜጠኛ ሪም አባስ በካርቱም እስረኞች መለቀቃቸውን በትዊተር ገፁ ላይ አስፍሯል።

    ይህ ምንም እንኳ ከገለልተኛ ወገን ባይረጋገጥም በሱዳን ውስጥ ለውጥ እየተካሄደ ነው ለሚሉ ማረጋገጫ ሰጥቷል።

  4. አል በሺር ከስልጣን መውረዳቸውን ሮይተርስ ዘገበ, አል በሺር ከስልጣን መውረዳቸውን ሮይተርስ ዘገበ

    የ X ይዘትን ይለፉት
    ይዘቱን X ይፈቅዳሉ?

    ይህ ጽሑፍ በX. የቀረበ ይዘት ይዟል። ገጹ ቴክኖሎጂዎች ወይም ኩኪዎች ሊኖረው ስለሚችል ገጹ ከመከፈቱ በፊት የእርስዎን ፍቃድ እንጠይቃለን። ፍቃድዎን ከመስጠትዎ በፊት የX ኩኪ ፖሊሲ እና የ ማንበብ ይፈልጉ ይሆናል። ይዘቱን ለማንበብ ‘እቀበላለሁ ቀጥል’ የሚለውን ይምረጡ።

    ማሳሰቢያ: በሌሎች ገጾች ላይ ላሉ ይዘቶች ቢቢሲ ኃላፊነት አይወስድም።

    የ X ይዘት መጨረሻ

    የሱዳን ፕሬዝዳንት የሆኑት አልበሺር ከስልጣን መውረዳቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። በአሁኑ ሰዓትም የሽግግር መንግሥት ምክር ቤት ለማቋቋም ምክክር ላይ መሆናቸው ተገልጧል። ቢቢሲ ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን መውረዳቸውን ያላረጋገጠ ሲሆን ይፋዊ መግለጫን በመጠበቅ ላይ ነው።

  5. ስለኦማር ሃሰን አልበሽር በጨረፍታ, ስለኦማር ሃሰን አልበሽር በጨረፍታ

    ሱዳንን ለ30 ዓመታት ስለገዙት ኦማር ሃሰን አልበሽርን ታሪክ በጥቂቱ

    • የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሃሰን አል ባሽር ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት በጨረፍታ በአረቦችና በእስራኤል መካከል በተደረገው የ1973 (እኤአ)ጦርነት በግብጽ ሰራዊት ውስጥ በመሆን ተዋግተዋል
    • በ1989 (እኤአ) በእስላማዊ እንቅስቃሴ አራማጆች በተደገፈ መፈንቅለ መንግሥት ስልጣን ያዙ
    • በ1990ዎቹ (እኤአ) የአልቃኢዳ መሪ ለነበረው ኦሳማ ቢን ላደን ጥገኝነት ሰጥተው ነበር
    • በ2009 (እኤአ) እርሳቸው ውድቅ ባደረጉት ዳርፉር ውስጥ ተፈጽሟል በተባለ የጦር ወንጀል በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ ተመሰረተባቸው። በዚህም በፍርድ ቤቱ የተከሰሱ የመጀመሪያው የሃገር መሪ ሆነዋል።
    • በ2005 (እኤአ) ለዘመናት በጦርነት ሲፋለሟቸው ከነበሩት የደቡብ ሱዳን አማጺያን ጋር ሰላም አወረዱ ውስጥ
    • በ2011 (እኤአ) ደቡብ ሱዳን እንድትገነጠል ያደረገውንና ሱዳን ከነበሯት የነዳጅ ማውጫ ጉድጓዶች ሦስት አራተኛውን እንድታጣ ያደረጋትን ሕዝበ ውሳኔ ፈቀዱ
    • ኦማር ሃሰን አል በሽር ልጆች የሌሏቸው ሲሆን ስለግል ሕይወትታቸውም የሚታወቀው ጥቂት ነው
    ኦማር ሃሰን አልበሽር

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images

  6. በካርቱም የሱዳን ጦር ኋይል መንገዶችን መዝጋቱ ተሰምቷል, በካርቱም የሱዳን ጦር ኋይል መንገዶችን መዝጋቱ ተሰምቷል

    ተቃዋሚ ሰልፈኞች

    በሱዳን ከፍተኛ የፕሬዝዳንት አልበሺር ከስልጣን እንዲወርዱ የሚጠይቁ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች መሰማት የጀመሩት ከወራት በፊት ነው። ዛሬ በዋና ከተማዋ ካርቱም የጦር ኃይሉ መኪኖች መንገድ መዝጋታቸው ተነግሯል።

  7. የሱዳን ጦር ኃይል መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል, የሱዳን ጦር ኃይል መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል

    እንደምን አረፈዳችሁ። በሱዳን የፕሬዝዳንት አል በሺር እጣፈንታን በተመለከተ የሱዳን ጦር ኃይል መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ቢቢሲ አማርኛ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ እየተከታተለ ያቀርብላችኋል።

    ፕሬዝዳንት አልበሺር

    የፎቶው ባለመብት, Getty Images