
የፎቶው ባለመብት, Reuters
የምስሉ መግለጫ, ቢቢሲ በአካባቢው ፍንዳታ ከደረሰ በኋላ ነዋሪዎች ተደናግጠው መሰባሰባቸውን አረጋግጧል።በደቡባዊ ኢራን በሚገኝ
ትምህርት ቤት ላይ አሜሪካ እና እስራኤል ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 148 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ።
የኢራን ፕሬዝዳንት ማሱድ
ፔዚሽኪያን “ኋላ ቀር ድርጊት ነው። አጥቂዎቹ ከፈጸሟቸው አሰቃቂ ድርጊቶች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል” ብለዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል በትምህርት
ቤት ላይ ጥቃት ስለመድረሱ ያሉት ነገር የለም።
የኢራን ቀይ ጨረቃ እንዳለው
በመላው አገሪቱ ቢያንስ 201 ሰዎች የሞቱ ሲሆን 747 ሰዎች ተጎድተዋል።
በጄኔቫ የሚገኙ የቀይ ጨረቃ
እና ቀይ መስቀል አመራሮች እንዳሉት፤ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ትምህርት ቤቱ ተልኳል።
በኢራን ሆርሞግዣን ግዛት፣ ሚንዳብ ከተማ በሚገኘው ትምህርት ቤት ላይ “ሦስት የሚሳዔል ጥቃት”
መፈጸሙን አንድ ባለሥልጣን ተናግረዋል።
ቢቢሲ በአካባቢው ፍንዳታ ከደረሰ በኋላ ነዋሪዎች ተደናግጠው መሰባሰባቸውን አረጋግጧል። ምን
ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ግን ማረጋገጥ አልተቻለም።
ኢራናውያን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ቁጣቸውን እየገለጹ ነው። አንድ ከኢራን ውጭ የሚኖሩ የአገሪቱ
ዜጋ ወታደራዊ እርምጃውን አውግዘው “የጦርነታቸው የመጀመሪያዎቹ ሰለባዎች በሚሳዔል የተመቱ 40 ታዳጊ ሴቶች ናቸው። ይሄንን ድርጊት
ነው የምታወድሱት?” ብለዋል።